በያዝነው አመት መስከረም 17 ተመርቆ ህዳር አካባቢ ትምህርት የጀመረው የከንቱዋቱ አንሷር መርከዝ ከረመዳን በፊት ባዘጋጀው ፕሮግራም ላይ ተማሪዎቹ የደረሱበትን ደረጃ ማሳየት ችሏል።
በአራት ወራት እንዲዚህ አይነት ተማሪዎችን ማፍራት ይቻላል።
አላህ ለተሻለው ይወፍቃቸው።
በሌሎች አካባቢዎችም በርካታ መሰል ት/ት ቤቶች ያስፈልጋሉ ሁሉም የበኩሉን ድርሻ ይወጣ፡፡
ይህን ማሳካት የሚቻለው ግዴታን በመወጣት ብቻ ሳይሆን ኃላፊነትን በመሸከምም ጭምር ነው።
﴿ وَٱلَّذِينَ جَٰهَدُواْ فِينَا لَنَهۡدِيَنَّهُمۡ سُبُلَنَاۚ وَإِنَّ ٱللَّهَ لَمَعَ ٱلۡمُحۡسِنِينَ ﴾ [العنكبوت - ٦۹]
{እነዚያም በእኛ መንገድ የታገሉ መንገዳችንን በእርግጥ እንመራቸዋለን፡፡ አላህም በእርግጥ ከበጎ ሠሪዎች ጋር ነው፡፡} [ዐንከቡት 69]
በመማር በማስተማርና በድጋፍ ላይ ያሉ ወንድዎቻችንን አላህ በሁለቱም አገር ስኬትን ይፃፍላቸው። ኣሜን!!