የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የአገልግሎቶቹን ክፍያ በቴሌብር በኩል መፈጸም የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር ተፈራረመ
የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የአገልግሎት ክፍያ ሥርዓቱን በማዘመን፤ የአገልግሎቶቹን ክፍያ በቴሌብር በኩል መፈጸም የሚያስችል ስምምነት ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በዛሬው ዕለት ተፈራርሟል።
በዚህም መሠረት የኤጀንሲው ባለጉዳዮች ያለምንም ውጣ-ውረድ እና እንግልት የመኪና ሽያጭ ውል፣ የስጦታ፣ የውክልና፣ የብድር፣ የማህበር ምስረታ እና ቃለ ጉባኤ የመሳሰሉ ከ27 በላይ አገልግሎቶቹን ክፍያ በቴሌብር መፈጸም እንዲችሉ መደረጉ ተገልጿል፡፡
ባለጉዳዮች ኤጀንሲው የሚሰጣቸውን የክፍያ ማዘዣ ቁጥር በመጠቀም፤ በቴሌብር መተግበሪያ ወይም በአጭር ቁጥር (*127#) የአገልግሎት ክፍያዎችን በቀላሉ መፈጸም እንደሚችሉም ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል፡፡
_
አዲስ ማለዳ