ትናንት ለሊት ከንግድ ባንክ የሌላችሁን ገንዘብ ለወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ፣ በማወቅም ይሆን ባለማወቅ የወሰዳችሁትን ብር መልሱ አለበለዚያ ግን ተጠያቂ ትሆናላችሁ እየተባላችሁ ነው። ግር የሚለው ግን ንግድ ባንክ እስካሁን ይህን በርካቶች የሌላቸውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ያወጡበትን ድርጊት በይፋ አለማሳወቁ ነው። "የሲስተም ችግር እንጂ የሳይበር ጥቃት አልደረሰብኝም" የሚል መግለጫ አሁን አውጥቷል። የተፈፀመበት ዝርፊያስ? ሌላው አለም ላይ ቢሆን መጀመርያ ድርጊቱ ይፋ ይደረጋል፣ ከዛም ምን ያህል ገንዘብ፣ በየትኛው አካባቢ ካሉ ተገልጋዮች፣ በምን መልኩ፣ የወሰዱ ሰዎች ላይ የሚወሰዱ አካሄዶች... ወዘተ የሚሉ መረጃዎች ቢያንስ ለደንበኞች ይነገራል። ምስል: ማህበራዊ ሚድያ @EliasMeseret 16.3K views12:51