#የአጋንንት ! #የዓይነ ጥላ! #የዛር መንፈስ! መራቅያ የብራና አስማተ ቅዱስ ሚካኤል ጸሎት ይህ | መርጌታ አለምአየሁ
#የአጋንንት !
#የዓይነ ጥላ!
#የዛር መንፈስ! መራቅያ የብራና አስማተ ቅዱስ ሚካኤል ጸሎት ይህ ነው::
#ይህ ጸሎተ ሚካኤል በቀደምቶቹ በብራና ላይ ተከትቦ ከትውልድ ትውልድ ሲተላለፍ ቆይቶ ይሄው እኛ ዘንድ ደርሷል::
በድርሳኑ እንደሚለው ለቅዱስ ሚካኤል የተሰጠ ልዩ እና ኅቡዓት አስማት ዲያብሎስን ድል መንሻ ነውና ልብ ይበሉ::
#እኛ እኮ በብዙ መንገድ የታደልን ግን ደግሞ በአጉል ፍርጃ ማንነታችን ያጣን ሰዎች ሆንን እንጂ የተሰጠን እና ያለን ነገር ብዙ ነው::
#ለረዥም ጊዜ በዚሁ ቤት አዲስ ነገር መላክ እና ማስተላለፍ ካቆምኩኝ ቆየሁ ይህ የሆነበት ምክንያትም ከአሁን በፊቱ በተሻለ መልኩ እውቀትን ለማቀበል በማሰብ ነውና ይቅር በሉኝ::
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ቶሎ ቶሎ እውቀቶችን ለማስተላለፍ እሞክራለሁ::ወዳጆቼም እንዲሁም ቤተሰቦቼ እንደበፊቱ በአጋንንት ወጥመድ ውስጥ ላሉ ይደርስ ዘንድ እንዲሁም በጸሎተ ሚካኤል በቤታቸው ከችግራቸው ይላቀቁ ዘንድ!
መልእክቱን ለወዳጆቻችሁ አጋሩ!
ገቢሩም:
#በንጽህና ጧት ጧት 3 ወይም 7 ጊዜ በውኃ ላይ ማድረስ
#በቅብዓ ቅዱስ ላይ ጸሎት በማድረስ የታመመው አካላችን መቀባት
#ስራ ባይሳካልን ጧት በባዶ ሆድ ጸሎቱን አድርሰን መሄድ
#እንዲሁም ለማንኛውም ችግራችን አስማተ ሚካኤል በቀይ ቀልም በልሙጥ ወረቀት ከነጠልሰሙ ጽፈን አክብረን ብንይዘው ይሆንልናል::
የቅዱስ ሚካኤል ጥበቃ አይለየን!
በአያቶቻችን የእጽዋት ጥበብ እና በፈጣሪ ኃይል፣ ከህይወትዎ ላይ ክፉ መናፍስትን እንዴት ማራቅ እንደምንችልና፣ እንዲሁም የብራና መጽሐፍት ጥቅማቸው በዚ ይዳሰሳሉ::
0912999705
0912999705