2022-03-12 20:40:30
ዐርፈዋል ይላሉ - ያልተረዱ ሁሉ፣
በዚህ ዓለም ወሬ - መች ኖረው ያውቃሉ?
ሞተዋል ይላሉ - ሳያወሩ ቢያዩ፣
ዓለምን ትተዋት - ዝምስ ካሉ ቆዩ።
ጠፋን ተጠፋፋን - እየለፈፍንና - እየለፈለፍነው፣
ግና ብናውቅበት - አፍ የተፈጠረው - ዝምም ለማለት ነው።
ጽድቅና ኩነኔ ቢያዝ ባይያዝም፣
ከክፉ ንግግር ይሻላል ማለት ዝም።
የማይጠቅም ወሬን - ሰርክ ከማቀበል፣
ከአባታችን ጋር - አብረን ዝም እንበል።
መርቆርዮስ የሚል - ሁለት ስም አውቃለሁ፣
አንደኛው አንገቱን
አንዱም አንደበቱን - ሰጥተዋል እላለሁ።
እንደምን ኃያል ነው - መርቆርዮስ 'ሚል ስም፣
ሰማዕት ያደርጋል - ባንገትም በአፍም።
ዝምታ ወርቅ ነው - ሲሉ ሰምቻለሁ፣
ጽድቅ መሆኑን ግን - በዐይኔ አሁን አየሁ።
ስንት ታሪክ እያለ - ካፋቸው ሚደመጥ፣
ዝም ብለው ዐረፉ - ለሊቅ ለደቂቁ - ቃል እንዳይጎረብጥ።
ስንት እውነት እያለ - ካፋቸው 'ሚለቀም፣
ስለሚልቀው ሐቅ - ጻድቁ አፋቸው - ከቶ አልተላቀቀም።
እውነታችን አልቆ
ተንጠፍጥፎ በንኖ - ለማውራት ስንቸኩል፣
እውነትን ሰንቆ
ዝም ያለ አንደበት - አለ በዚህ በኩል።
መርቆሪ መርቆሪ - ብለን ብንጣራ - 'አቤት'ህ ዝም ነው፣
ለነባቢ አፋችን - የዝምታህ ጸጋ - ረድኤት ይሁነው።
6.5K views17:40