2022-05-07 19:28:24
ሰላም !
አንዲት ሙስሊም ሴት በፌደራል ፍርድ ቤት ባለቤቷ ፍቺውን እየተቃወመ የፍቺ ውሳኔ የተሰጠ ሲሆን ይህ ፍቺ በሸሪአ ሕጉ መሰረት እንዴት ይታያል?
ይህች ሴት በድጋሚ በሸሪአ ፍርድ ቤት ፍቺ በድጋሚ ብትጠይቅ በድጋሚ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ /res judicata/ ይሆንባት ይሆን?
በእርግጥ ይህ ጥያቄ የሸሪዐ ፈትዋ ጥያቄ ያዘለ በመሆኑ ለሀይማኖቱ ልሂቃን-ኡለሞች መቅረብ ያለበትጥያቄ ነው ።
በግልጽ እንደሚታወቀው በሸሪአ ህግ ፍቺ እራሱን የቻለ ሕግ እና ስርዐት አለው። በሸሪዐ ሕግ ፍቺን የመፈጸም ስልጣን as a rule ለወንድ የተሰጠ ሲሆን በተለየ ሁኔታ exception ሴቶች በጋብቻው መብታቸው በማይከበርበት ሁኔታ ወይም ኹልዕ በተባለ ስርአት ፍቺ ለመፈጸም ለቃዲ ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ።
በፌደራል ፍርድ ቤት የፈረሰን ጋብቻ በተመለከት የሽሪዐ ሕግን ሥርዐት አሟልቶ ጋብቻው ፈርሷል እንደማይባል የሀይማኖቱ ልሂቃን ሀሳብ ይሰጣሉ።
Resjudicata /ፍርድ በተሰጠበት ጉዳይ በድጋሚ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄን/ በተመለከተ በፍ/ሥ/ ሕግ ቁጥር 5 በተቀመጠው ፍርድ በተሰጠበት ጉዳይ ላይ በድጋሚ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ
በቀጥታ ከሕጉ አንጻር ካየነው በድጋሚ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ ሊያስብል ይችላል። በኢፌድሪ ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በተሰጠ ውሳኔ መሰረት አንድ ጉዳይ በድጋሚ የቀረበ ነው የሚባለው ፍሬ ነገሩ ወይም ተከራካሪዎቹ ተመሳሳይ ከሆኑ እንደሆነ ውሳኔ ሰጥቷል።
የሸሪዐ ፍርድ ቤቶች ጉዳዮችን የሚያሳልጡበት እና ሥነስርዐት የሚያስኬዱበት ሕግ የፍ/ሥ/ሕግ በመሆኑ ጉዳዩ በድጋሚ የቀረበ ነው ሊባል የሚችልበት እድል ሰፊ ነው።
የሸሪዐ ፍርድ ቤቶች ፍርድ የሚሰጡበት መሠረታዊ ሕግ ቁርአን እና ሀዲስ ከፍታብሄር ከሥነሥር ሕግ ጋር የሚጋጩ ቢሆን እንዴት ዳኝነት መስጠት አለባቸው የሚለው ገና የሕግ መፍትሄ ያላገኘ የምርምር ርዕሰ ጉዳይ ነው። ለምሳሌ በሸሪዐሕግ መብት በተለይም የወራሽ መብት በጊዜ ገደብ የማይደረግበት ሲሆን በሽሪዐ ፍርድ ቤቶች የውርስ ጥያቄ በሚቀርብበት ጊዜ የሥነሥርዐት ሕግን መሰረት ያደረገ መቃወሚያ ሲቀርብ እያስተዋልን ነው።
በተመሳሳይ በእህታችን የቀረበው ጥያቄ ጥናት እና ምርምር ሊደረግበት የሚገባ ጉዳይ ነው። እንደኛ እምነት ጉዳዩ ራስን ነጻ ማድረግ /innocence برائت ذمه/ መርህ ጉዳዩ ለሸሪዐ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት። ሸሪዐ ፍርድ ቤት በድርሚ የቀረበ የዳኝነት ጥያቄ ነው በሚል ውሳኔ ቢሰጥበት እንኳን ተቋማዊ ባልሆነ መልኩ ጥያቄው ለግለሰብ ቃዲ ቀርቦ ያሸሪዐ ፍቺውን ለማግኘት ጥረት ማድረጉ አስፈላጊ ነው።
በዚህ መልስ ላይ በሸሪዐ ጉዳይ የቀረበው ምላሽ የመጨረሻ ተብሎ ሊያዝ የማይገባው በምሆኑ በጉዳዩ ላይ ፈትዋ መስጠት የሚችሉ አሊም ለሚጠይቅ በኢንቦክስ ስልክ ለመላክ እንችላለን።
ለጥያቄው እናመሰግናለን።
411 viewsedited 16:28