2022-09-27 21:27:17
#የእምነትና_የፍርሃት_መልክ “ኢየሱስም፣ ‘ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም’ ተብሎ ተጽፎአል' ሲል መለሰለት።”
— ማቴዎስ 4፥4 (አዲሱ መ.ት)አለም አሁን በጤና ላይ እየሰራች ያለችው ለምን ይመስላችኋል ?
አለም በአሁን ሰዓት በጤና ላይ እየሰራች ያለውን ያህል ከዚህ በፊት ስትሰራ አልተስተዋለም። የአሁኑን ያህልም ለጤና የተጠነቀቀችበት ጊዜ አልነበረም። ትልልቆቹ እና ዋነኞቹ የምግብ አምራቾች እንኳን ሰዎች ጤነኛ ሆነው እንዲቆዩ ለመርዳት በታዋቂ የምግብ አቅርቦቶች ውስጥ ያለውን የስኳር ፣ የጨው ፣ የዘይት እና የተለያዩ የንጥረ ነገሮችን መጠን እየቀነሱ ነው ። ይሁን እንጂ ይህ ሁሉ ጥረት እየተደረገ አሁንም ተመጣጣኝ ያልሆኑ ነገሮችን በልተው ጤናቸውን ስጋት ላይ የሚከቱ አልጠፉም።
#ታድያ ይሄ ከመንፈሳዊ ህይወት ጋር ምን ያመሳስለዋል??
ከላይ ሰለ ስጋዊ መብል እንዳወራነው በመንፈሳዊ ህይወትም ተመሳሳይ ነው።
እንደ ክርስቲያን ትክክለኛውን የእግዚአብሔርን መረጃ፣ ትምህርት እና ሐሳብ መመገብ አለብን።
“እንግዲያስ እምነት የሚገኘው መልእክቱን ከመስማት ነው፤ መልእክቱም በክርስቶስ ቃል ነው።”
— ሮሜ 10፥17 (አዲሱ መ.ት)
#ለእምነትህ
የእግዚአብሔርን ቃል በመመገብ ጤነኛ የሆነ እምነትን በህይወትህ ልታሳድግ ይገባል።አንዳንድ ክርሰቲያኖች ግን እምነታቸውን ከመመገብ እና ከማጠንከር ይልቅ ፍርሃትን በህይወታቸው ይመግባሉ።
ለተሳሳተ መረጃ እና ሐሳብ ትኩረት ሲሰጡ ፍርሃትን ይመግባሉ።ፍርሃት እንዴት ሊመጣ ይችላል?
ሰዎች ለሚናገሯቸው አሉታዊ ነገሮች አላስፈላጊ ትኩረት ስትሰጥ ወይም አንድም ጥሩ ነገር ከማይታይባቸው፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ከሌላቸው፣
የእግዚአብሔርን መንፈስ እናውቃለን ከሚሉ ነገር ግን ከማያውቁት ሰዎች ጋር ስትገናኝ በመንፈስህ ለይ የእግዚአብሔርን ቃል በመመገብ የገነባኸውን እምነት እነርሱ በቀላሉ እንዲያፈርሱ እና ከአመንከው ነገር ጋር ደግሞ ወደ መጨባበጥ እንዳትመጣ ከዛ ነገር ጋር ያለህን የመጨባበጥ ቀጠሮ ይሰርዙብሃል ።#አያችሁ
እምነት የተስፋችሁ ብቸኛው ማረጋገጫ ነው።በመንፈሳዊ ህይወት በ እግዚአብሔር ልጅ በክርስቶስ ኢየሱስ የመስቀል ሥራ የተፈፀመውን ጉዳይ ለመቀበል አንተ በጊዜው እና በቦታው አልነበራችሁም ወይም ኢየሱስን ምድር ላይ እያለ ያገኙት ደቀመዛሙርት የእናንተንም ጎረቤት ወይም ደግሞ ዘመድ አይደሉም ስለዚህ
ከየትኛውም መንፈሳዊ ነገር ጋር በአካል መተዋወቅ እና መጨባበጥ የምትችለው በእምነት ብቻ ነው።የእምነት ምንጩ የእግዚአብሔር ቃል ነው።
ስለዚህ አስተውል የተሳሳተን መረጃ መመገብ የሚያስከትለው ውጤት በአንድ ጀምበር ላይታወቅና ላይብራራ ይችላል።አንድ ሰው ከእግዚአብሔር እየራቀ በሚሄድበት ጊዜ እየደከመ እየሞተ እና ከክርስቶስ ህይወት እየወጣ እንደሆነ ብዙ አደባባይ የሚገለጡ የኀጢአት ልምምዶችን ማድረግ እስኪጀምር ድረስ ምን እንደጣለ ፣ ምን እንደጎደለው ላይገነዘብ ይችላል። ይህ የሚሆንበት ምክንያት የመጀመሪያውን እምነት ባለመመገቡ ምክንያት ነው።
#ከዚህ በኋላ በዚህ ሰው መንፈሳዊ ህይወት ምን ይከሰታል?
ይህ ሰው ከዚህ በኃላ እንደ ቀድሞው ለመንፈሳዊ ነገሮች ቀናተኛ እና ንቁ መሆን አይችልም።
በመቀጠልም ህይወቱን ከእግዚአብሔር እቅድ ፈጽሞ በተለየ አቅጣጫ መምራት ይጀምራል።
ስለዚህ ለትክክለኛው ከእግዚአብሔር ቃል ለሆነ የመገለጥ እውቀት ፣ የቃል ብርሃን ትኩረትና ትልቅ ቦታ በህይወታችን ልንሰጥ ይገባል።ሁል ጊዜ ከቃሉ በመቆራኘት እራስህን ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣው ቃል መኖርን አስለምድ።
— ዮሐንስ 15፥7 (አዲሱ መ.ት)“በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ፣ የምትፈልጉትን ማንኛውንም ነገር ለምኑ፤ ይሰጣችኋልም።”
ዮሐንስ 14 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯²¹ የሚወደኝ ትእዛዜን ተቀብሎ የሚጠብቅ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል፤ እኔም እወደዋለሁ፤ ራሴንም እገልጥለታለሁ።”
…
²⁴ የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም። ይህ የምትሰሙት ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።
ጌታ ኢየሱስ ይባርካችሁ
17/01/15
@hayorevival
@hayorevival
@hayorevival
@hayorevival
99 viewsedited 18:27