ቀያይ ሴጣኖቹ መድፈኞቹን ረተዋል!
በስድስተኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ ተጠባቂ መርሐ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ 3 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የአርሰናልን #ያለመሸነፍ ጉዞ ገተዋል።
√ ማርከስ ራሽፎርድ ( 2X ) እንዲሁም አዲሱ ፈራሚ አንቶኒ የቀያይ ሴጣኖቹን የማሸነፊያ ግቦች ከመረብ አሳርፈዋል።
√ ቡካዮ ሳካ የመድፈኞቹን ብቸኛ እና አቻ ያደረገች ግብ ማስቆጠር ችሎ ነበር።
√ ቡካዮ ሳካ በዘንድሮው የውድድር ዓመት በሊጉ የመጀመሪያ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።
√ ማርከስ ራሽፎርድ ባለፉት አራት የሊግ ጨዋታዎች ላይ ሶስት ጎል ሲያስቆጥር ሁለት ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ አቀብሏል።
√ አንቶኒ በመጀመሪያ ጨዋታ ግብ ማስቆጠር የቻለ በእድሜ ትንሹ ብራዚላዊ ለመሆን ችሏል።
√ #አርሰናል አሁንም ሊጉን #ሲመሩ ከተከታያቸው ማንችስተር ሲቲ በአንድ ነጥብ በልጠው ይገኛሉ።
√ ተከታታይ ጨዋታዎችን ያሸነፉት ማንችስተር ዩናይትዶች በአስራ ሁለት ነጥብ #አምስተኛ ደረጃን ይዘዋል።
√ በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር #አርሰናል ከ ኤቨርተን እንዲሁም #ማንችስተር_ዩናይትድ ከ ክሪስታል ፓላስ የሚገናኙ ይሆናል።