Get Mystery Box with random crypto!

ሀበሻዊ ጥበባት

የቴሌግራም ቻናል አርማ habeshistanyesetlij — ሀበሻዊ ጥበባት
የቴሌግራም ቻናል አርማ habeshistanyesetlij — ሀበሻዊ ጥበባት
የሰርጥ አድራሻ: @habeshistanyesetlij
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 204
የሰርጥ መግለጫ

እኔ የምፈራው ሞት ሞትን ቀድሞ መሞት!!!

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-11-18 21:36:03 "ፊት"!!! ያፈቀርኩ እለት




ካሊድ (ሀበሺስታን)



2


የምንታወቀው በምንለብሰው ቲሸርት አይደለም። እኔ የምታወቀው << ያ እንደ ሽማግሌ የሚያደርገው ልጅ>> በሚለው ነው። በቲሸርት የማልታወቅበት ምክንያት ቲሸርት ስለምሸያይር ነበር ሀብታም እንደነበርን በዚህ ተረዱኝ የልብስ ሀብታም ማለቴ ነው።

እንደውም አንድ ጊዜ ነጭ ቲሸርት ሆና እላይዋ ላይ በፊት ለፊት በትልቁ ቀይ የልብ ቅርፅ ምስል እና ከስሩ ''I LOVE MAMA"" የሚል ቲሸርት ከውጭ መጥቶልኝ ሰኞ ቀን ለብሼው ሄድኩ። የሰው ሁሉ አይን ሲያርፍብኝ ልቤ ጮቤ እረገጠች። ነገር ግን ፅሁፉን ያነበበው ጥቂቱ ስለነበር በቀዯ ልብ ቅርፅ ምክንያት ብዙ ተወራብኝ ፤ከተወሩት መሀል:-

<<አፍቅሮ ነው እኮ፣ በዚህ እድሜው ምነው ተንቀዠቀዠ፣ እዮኝ እዮኝ አበዛ>> ከዚህ መሀል ያምራል ያለኝ መኖሩን እጠራጠራለሁ።


የክፍሉ ጭምት ተማሪ ነኝ። አላወራም ግን፤ ፈዛዛ አይደለሁም። ሁሉም ተማሪ የሚያደርገው ነገር ያስገርመኝ ነበር እናም ከእራሴ ጋር እያወራሁ በሰው ሁኔታ እስቅ ነበር ። ለምሳሌ ማትስ መምህራችን መነፅር የሚያደርጉ አጭር መምህር ነበሩ። አጥረው ቦርዱ ላይ ከግማሽ ዝቅ በሚለው ቦታ ላይ ከማስተማራቸው ይልቅ ከአፍንጫቸው ዝቅ አድርገው በሚያደርጉት መነፅር መፅሀፋቸውን ከላይ በአይናቸው እኛን የሚያዮን ነገር ያስገርመኝ ነበር።

አንድ ጊዜ ከክፍሉ ተማሪ እያስወጡ እንዲያስረዳ ሲጠይቁ እኔን እንዳይጠይቁኝ ስፀልይ ፀሎቴ አልሰመረ ኖሯል፤ <<አንተ ጋግርታም ና ውጣ እስኪ አስረዳ>> አሉኝ። ወጣሁ ቾክ ያዝኩ የገረመኝ ልክ እንደሚያስረዳ ሰው ትልቅ ቾክ መያዜ። ለነገሩ ከተሳካልኝ ለመስረቅ ነበር ምንም ለማልፅፍበት ለምን ቾክ መውሰድ እንደሚያስደስተኝ አይገባኝም።

ቦርዱ ላይ የተፃፉት ቁጥሮች አፈጠጡብኝ። እጄን ቦርዱ ላይ ሰቅዬ መልሱ ከሰማይ ይወርድ ይመስል መጠባበቅ ያዝኩ። ቄሱም ዝም መፅሀፉም ዝም ሆነ ነገሩ። መምህሩ ዝም አሉኝ። አሁን ማን ይሙት ካላጡት ተማሪ እኔን ማስወጣት ምን ይሉታል! በቃ እኔ ችሎታዬ አንደኛ መውጣት ብቻ ነው። ለምን አይተውኝም እያልኩ በሀሳብ ስሰምጥ <<ና ተቀመጥ ሰዐት አታቃጥል ያቃጥልህ የሚያቃጥል ነገር>> አሉኝ ። ወደ እኔ እየመጡ እንዳልመታ ሸሸት ብዬ ወንበሬ ላይ ተቀመጥኩ÷ ደንግጬ ቾኩን የት እንደጣልኩትም አላስታውስም። ቀና ብዬ ቦርዱን ስመለከት የእጄ ላብ ዱካ መስሎ ታግሟል።


ጐበዝ ተማሪ ከሚባሉት ጐራ አልመደብም። ወይም እዮኝ እዮኝ ባይ ተማሪም አይደለሁ። በፈተና ወቅትም ከሚኮርጁት እንዝላል ተማሪዎችም አልመደብም። የግሩፕ ስራ ሲሰጥም የበኩሌን አደርጋለሁ። ብቻ ግን በፈተና ወቅት ከማንም በላይ ጥሩ ውጤት የማመጣ እኔ ነበርኩ ።

ከክፍላችንም አንደኛ ወይ ሁለተኛ ደረጃ ለመውጣት የሚገዳደረኝ አልነበረም። አስማት ሊመስላችሁ ይችላል ግን እኔም እንዴት እንደሆነ አላውቅም።

የምቀመጠው ከክፍሉ መግቢያ በር አጠገብ ነበር። እዚህ ቦታ ላይ በምርጫዬ ባልቀመጥም ወድጄው የምቀመጥበት ቦታ ነው። የወደድኩት ደግሞ ክፍል ውስጥ ብሆንም ካለማንም ከልካይ ውጪ ያለውን ነገር መኮምኮሜ ነው መምህሩ ሲያስተምር ልቤም አይኔም ውጩን ያማትራል።

ከኋላዬ አብዱልሀኪም አለ፤ አብዱልሀኪም እናቱም አባቱም መመህር ሲሆኑ እሱ ግን የአቦጊዳ ሽፍታ ነበር። እውቀት በዞረበት ያልዞረ እንደውም ማጋነን ካልሆነ ደደብ ከማለት አንተ አብዱል ሀኪም ነገር ነህ ብባል እበሳጫለሁ።

ደደብነት እራሱ አብዱልሀኪምን ደደብ ብሎ ነው የሚሰድበው። ታዲያ ድድብናው ትምህርት ላይ ነው እንጂ እሳት የላሰ ሌባ ነው!! እንደውም አባቱ ብር እየቆጠሩ ሲያዮት ፈርተው ወደ ኪሳቸው ይመልሱ ነበር። ሁሌም ማታ ይገረፋል ምክንያቱም ሁሌም ይሰርቃል። አባቱ ከውጭ እንደመጡ ቅድሚያ ስራቸው መታጠብ ወይ መመገብ አይደለም <<ስማ አብዱልሀኪም ያንን የቆዳ አለንጋ አምጣ >>ይባላል ባመጣው አለንጋ ይገረፋል።

ታዲያ ሁልጊዜም ከመገረፉ የተነሳ አባቱ አንድ አንድ ጊዜ እንደገቡ ይገርፉታል። <<አባዬ ምን አደርግኩ>> ይላቸዋል <<አልሰረቅክም እንዴ>> ይሉታል << አዎ>> ይላል <<እንዴት ሌላ ዘዴ አመጣሽ ማለት ነው>> ብለው ይገርፉታል። አባቱን ከሚሰርቀው በላይ የሚያናድዳቸው ታዲያ ሲገረፍ ድምፅ እውጥቶ አለማልቀሱ አይደለም አንዲት የእንባ ጠብታ አለመውጣቷ ነው። የሆነ ቀን ለምን አታለቅስም ብለው እንደገረፉት ነግሮኛል። የሆነ ቀን ቤታቸው ሄጄ ሲገረፍ ደረስኩ። እስኪጨርስ ቆሜ እየጠበቅኩት አለማልቀሱ አስገርሞኝ አንገቴን አስገብቼ ስመለከት ፊት ለፊት ከተከፈተው ቴሌቪዥናቸው ላይ የህንድ ፊልም እያየ ስመለከተው <<እኚህ ሰውዬ ፀበል እያጠመቁት ነው ወይስ መሳጅ እያደረግኩት>> ብዬ ግራ ገብቶኝ ነበር።

ከዚህ በላይ ግራ ያጋባኝ ተገርፎ ሲጨርስ <<ሀበሽ እንሂድ>> ብሎኝ ምንም እንዳልተፈጠረ ይስቃል። <<ምን ሆነሀል የምትስቅ ቀልድ ሲነግሩህ የቆየህ ነው እኮ የምትመስል>> ስለው ቆም ብሎ ኪሱን ዳብሶ የወረቀቷን አንድ ብር አውጥቶ አሳየኝ። <<ምንድን ነው>> ስለው <<እየገረፈኝ ሲዘናጋ ሰረቅኩት>> ብሎኝ ሳይጨርስ አባቱ ና አንተ ሌባ እያሉ ወደ እኛ ሲመጡ ተመለከትኩ። ዞር ስል አብዱልሀኪም አጠገቤ የለም መኪና እራሱ እንደሱ መሮጡን የተጠራጠርኩት የዛን ቀን ነው። ከኑግ የተገኘህ ሰሊጥ አብረህ ተወቀጥ ነውና እኔንም እንዳይመቱኝ እግሬ አውጭኝ አልኩ ብዙ ተከትለውን ሲደክማቸው ቆይ ማታ ትመጣ የለ ብለው ዝተው ተመለሱ።




ይቀጥላል…………





@Habeshistan
439 views18:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-16 20:25:55 "ፊት"!!! ያፈቀርኩ እለት


ርዕሱ ቅኔ ነው!!!


ክፍል 1



እንተዋወቅ ሀበሽ እባላለሁ የስድስተኛ ቢ ክፍል ተማሪ ነኝ።ሲጋነን ወፍ ሳይንጫጫ፣ ለማኝ ሳይፀዳዳ እኔ የትምህርት ቤታችን አጥር የምትገኝ አንዲት ድንጋይ ላይ ተቀምጬ የትምህርት ቤቱ በር መከፈቱን የምጠባበቅ ተማሪ ነበርኩ። በአካባቢው ድቡልቡል እና ሸካራ ድንጋይ በበዛበት ይህቺ ጥቁር ጠፍጣፋ ድንጋይ ማን እንዳመጣት አላውቅም። ከሁሉም የሚገርመኝ ለሀበሽ ተብላ ከሰማይ የወረደች ይመስል ከእኔ ውጪ ማንም አይቀመጥባትም።

አንድ ቀን እንደለመድኩት በጠዋት በሌሊት ብለው ይቀላል ወደ ትምህርት ቤታችን ገሰገስኩ። ልጅ እና ፊት አይበርደውም እንዲሉት ሀሩር የሆነ ያህል ነፋሱን እየቀዘፍኩት ስሄድ እንዲች ብሎ አይበርደኝም ነበር።ትምህርት ቤታችን በር ጋር ስደርስ እና የትምህርት ቤታችን ጥበቃ መብረቅ እንደመታው ሰው ድርቅ አሉ። ምን አስደነገጣቸው ብዬ ስፈላሰም ብድግ ብለው <<አሀ ጌታው ፍርድ ቤት ጉዳይ እንዳለው ከሳሽ በጠዋት ለመምጣት ማንም እይቀድምህም አይደል! ይሄው ወንበርህ>> አለኝ ድንኳን የሚያህለውን ፎጣውን እየጐተተ ወደ ሌላ ድንጋይ እየተሸጋገረ።


ለካ የደነገጠ ድንጋዬ ላይ ስለተቀመጠ እና ስለመጣሁበት ነበር። ጥበቃው ጥርሱን እየፋቀ አላፊ አግዳሚውን የተቀደደች ኮፍያውን ቀና እያደረገ ቁጭ ብድግ እያለ ሰላም ይላል። ዞር ሲሉ <<ሰው መስሎሀል>> ይለኛል። አልሰማውም.... እንደማልሰማው ሲያውቅ <<ጋግርታም ምን ትለጐማለህ አታወራም እንዴ?>> ብሎ እየተበሰጫጨ ገባ። ምን እንዳበሳጨው ባይገባኝም ሀሜቱን ባለመጋራቴ መሰለኝ። ወይም የድንጋይ መቀመጫ እና የእናት ሞት እየቆየ ይቆረቁራል እንዲሉት የተቀመጠበት ድንጋይ ቆርቁሮት ይሆናል።

ፀጉሬን ሙልጭ አድርጌ በምላጭ የምላጭ፤ እየዘመንኩ ሄጄ በማሽን መስተካከል የጀመርኩ የአምስተኛ ክፍል ተማሪ ሆኜ ነው። እንደውም ከቤተሰብ መላምት ተነስቼ ስገምት ፀጉሬ አሁን ዞማ የሆነው ዞማ ስል የሚቃወሙ ቢኖሩም እደግመዋለሁ ዞማ የሆነው እስከዛ እድሜዬ በማሽን ስላልተነካሁ ነው ይባላል አሉ ነው አሉባልታ ከግነት ጋር ተቀላቅሎበት ቂ ቂ ቂ ቂ ።


በንፅህናዬ አልደራደርም። ጥንቅቅ ብዮ ኖርማል ፀጉሬን ተጣጥቤ ቅባት ተቀብቼ ነው ከቤቴ የምወጣው ። የግል ንፅህና ጠብቁ እየተባለ ሲነዛ ምሳሌ ነበርኩ። አንድ ጊዜ እንደውም የጥፍር ንፅህና ተብሎ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር የዚያን ሁሉ ተማሪ ጥፍር እየተመለከቱ ግማሹን << ምን ያዝረከርክሀል>> እያሉ ሲማቱ የእኔ ተራ ደርሶ ጥፍሬን ሲያዮ ቀና ብለው ፊቴን ተመለከቱና <<ማን ነው ስምህ>> አሉኝ ። <<ሀበሽ>> አልኩ <<ጥፍርህን ወደ ውስጥ በጣም ስለቆረጥከው ትንሽ አሳድገው>> ብለውኛል። እኔን የገረመኝ ግን ምን ያህል ስራ ቢፈቱ ነው ጥፍሩን ሲበላ የሚውል ውሪ ሁላ ጥፍር የሚያዮ የሚለው ነበር ወይስ ደሞዛቸው ጥፍር ከማየት ጋር ተያያዥነት አለው?


የምለብሰው የደንብ ልብስ ሸሚዙ ወደ ቀይ የሚያደላ እና ብሉ ብላክ ሱሪ ዮኒፎርሜ ባያምርብኝም አያስጠላብኝም። ረጅም ስለነበርኩ ሱሪውን እንደ ረጅም ቁምጣ ነበር የምጠቀመው ብል ግነት አይሆንም። ሸሚዙም ቢሆን ለጉራ ወደ ክንዴ ሰብሰብ ያደረግኩት እንጂ ያጠረኝ አይመስልም ። እንደዚህ አጥሮኝ ሌላ የማላሰፋበት ምክንያት አይገባኝም የእኔስ ይሁን ቤተሰቦቼ ግን አያዮኝም ነበር ወይስ አሰፉልኝ ያላለ ቢመቸው ነው ብለው ይሆን?

የምለብሰው የደንብ ልብስ ሸሚዙ ክፍት ስለነበር እንደ ጃኬት እጠቀመዋለሁ። ቲሸርት የፈለግነውን እንለብስ ስለነበር ልብሶቼ ሁሉ ቲሸርት ቢሆኑ እመኝ ነበር።ምክንያቱም ባለሀብትነታችንም ድህነታችንም የሚመዘነው እና የምናሳየው በቲሸርት ብቻ ነው። ቅዳሜ እና እሁድም ዮኒፎርሙን ሳያወልቅ ሰኞ የሚደርስባቸው ተማሪዎች ስለነበሩ የምንታወቅ የምንመዘን በቲሸርት ነበር።

ያ ቀይ ቲሸርት የሚለብሰው ሲባል ሁልጊዜም ከዮኒፎርሙ ውስጥ ቀይ ቲሸርት የሚለብሰው ዮሀንስ ነው። በሁሉም ተማሪ አዕምሮ የሚከሰት ሌላ ቀይ የሚለብስ ካለ ደግሞ ለመለያ አንድ ነገር አይጠፋም ያ ንፍጣሙ ይባላል የዛኔ ይፀድቃል።

ከተማሪው ብዙ ለየት የሚያደርጉኝ ነገሮች አሉ ከእነሱም አንዱ ፅዳት እና በዋናነት ዝምተኛነቴ ነው ። በሰፈሩ የምለይበት ደግሞ ከትልልቅ ሰው ጋር ብቻ ነበር የምግባባ። እኩዮቼ ጋር ብውልም የሚጫወቱት ጨዋታ ያስገርመኝ ነበር ምኑ ደስ ብሏቸው ነው እል ነበር። እግር ኳስ እንጫወት ብለው እስከ ሜዳ ሲሯሯጡ እኔ ቀስ ብዬ ስለምሄድ ዘግይቼ ነበር የሚጫወቱበት ሜዳ ላይ የምደርስ። ደርሼም ራቅ ብዬ ከሜዳ ውጪ ስለምቀመጥ አጠገቤ የልብስ መዐት ተደርድሮ ነበር የሚታይ የዚያ ሁሉ ልብስ ጠባቂ ነበርኩ።




ይቀጥላል……………




@Habeshistan
322 views17:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-25 18:34:02 ስለነበር ለምን እንደዚህ አድርጐ……… በዚህ አስበይዶ…… እያልን በማያገባን ነገር እያቦቀነጥን ሳናስበው ሰፈራችን ደረስን።


በውሎዬ አመሻሽ ስለገጠመኝ የአራዳ ልጅ እና የማላውቀው ወንድሜ እያሰብኩ በከፊሉ እየሳቅኩ በከፊሉ እያዘንኩ ወደ ክፍሌ ገባሁ የእኔ ጠባቧ አለም በፀጥታ ጠበቀችኝ በጀርባዬ ጋደም አልኩ።



@Habeshistan
369 viewsedited  15:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-25 18:32:20 //በውሎዬ አመሻሽ//

ካሊድ (ሀበሺስታን)

ስራዬን ጨርሼ ከአንድ ባለእንጀራዬ ጋር ከስራ ቦታ እየወጣን ነበር።

ወደ ታክሲ ተራ የምታደርሰዋን ቀጭኗን መንገድ በውስጤ <<ታክሲ እናገኝ ይሆን አይይይ አይመስለኝም>> እያልኩ ነበር የወረድናት።

ቀጭኗን መንገድ ጨርሰን ታክሲ ወደመያዣው ልናዘቀዝቅ መንገዴን ሳሰናዳ <<እእእ አንድጊዜ የሆነች ነገር እናስጨርስ>> አለኝ በጠያቂ አንደበት ደግሞ የሆነች ነገር ምንድን ናት? ብዬ እያሰላሰልኩ አስፓልቱን ተሻግረን አንድ ባለ 3 ፎቅ ደርብ ያለው ህንፃ ውስጥ ዘለቅን።

ቤቱ ኢንተርኔት ቤት ነው (ኢንተርኔት ካፌ) የሚሉት። ቤቷ ጠባብ ናት። እንደገባን በስተቀኝ አልጋ የሚያህል ሶፋ ተጋድሞ ተቀመጡ እያለ የሚጋብዝ ይመስላል። ነገር ግን ሶስት ሰዎች ብቻ እንደ ሱሉልታ መሬት አስፍተው ይዘውት ሌላ ሰው ለመጨመር አይጋብዝም


ባለእንጀራዬ ግን ትንሽ ቦታ ስላገኘ ሰርስሮ ገብቶ ተቀመጠ።
እኔም ግራ ቀኝ ስገላምጥ በስተግራ ሶስት ኮምፒውተሮች ተገጥግጠው የተጠቃሚ ያለህ የሚሉ ይመስላሉ። መቀመጫ ወንበር ባለመኖሩ ለኮምፒውተሩ ተጠቃሚ ተብለው የተዘጋጁት ሶስት ወንበሮች ውስጥ ተሽከርካሪዋን ወንበር መርጬ ተቀመጥኩ።


የአጋጣሚ ነገር ሆኖ ዛሬ እጄ ላይ መፅሀፍ ሳይሆን ክስ እንዳለበት ሰው ካኪ ይዤ ነው ከስራ የወጣሁት።

ባለእንጀራዬ ስልኩን ይዞ የማላዬውን ነገር እያዬ ሳቁን ይለቀዋል። እንደገና ቆይቶ የያዘውን መፅሀፍ ገልጦ ሙሉ ትኩረቱን እሱ ላይ አድርጐ ከእኔ ጋር በሀሳብም በመንፈስም ተለያየን ።

በዚህ መሀል አንድ ኢንተርኔት ተጠቃሚ መጣና ተሽከርካሪ ወንበሯን አስለቀቀኝ ተመችቶኝ ስለነበር ቅር እያለኝ ሌላ የማይሽከረከር ወንበር ላይ ተቀመጥኩ።

ከፊት ለፊቴ ያው ሲጋነን የምድር ወገብ የሚያህል ጠረጴዛ የቤቱ ወለል ላይ እንደተጋደመ አስተዋልኩ። ከጀርባው አንድ ቀይ ልጅ የማይገባኝን መዝሙር ይሁን ሙዚቃ ከፍቶ እየተዝናና ደንበኞቹን ያስተናግዳል። ዘፈኑ ወይ መዝሙሩ ብቻ የተከፈተው ነገር ያልገባኝ ልብ ብዬ ስላልሰማሁት ነው።

የቤቱ ደንበኛ ብዙ ነው ደንበኛ ክቡር ነው የሚለው መሸንገያ ቃል ባይለጠፍም ሰው ወደዚህ ቤት መትመሙን አልተወም። እንደዚህ ደንበኛ የበዛው ኢንተርኔት ቤት ሳይሆን ኢንተርኔት ካፌ ካፌ የምትለዋ ስባው ይሆን የሀገሬ ሰው እንደሁ ገር ነው ትንሽ ነገር ትደልለዋለች።

ከደንበኛው መሀል ግማሹ ፅሁፍ ያስፅፋ፣ ግማሹ ኮፒ ይላል፣ እኝን ይህንን ያህል ደቂቃ እንድንጠብቅ ያደረገን የሆነችዋ ነገር ከበድ ያለች ነገር ናት ብዬ መጠባበቅ ጀመርኩ።

በመሀል ሰው እየጨረሰ ሲወጣ ሶፋው ላይ ለመቀመጥ እድል አገኘሁ ሄጄ ሰፋ አድርጌ ያዝኩ። ለእኔ ብቻ ሳይሆን ለካኪዬም ሰፋ ያለ ቦታ ሰጠኋት።


ለካ ሰው እንደዚህ በወረፋ ይጠባበቅ የነበረው ወደ ውጪ ለመሄድ ዲዢ ይሉትን ነገር ለማስሞላት ኖሯል።

<<……… አሀ ወዳጄ አንተስ ለምን አትሞላም?>> አለኝ ባለ ኢንተርኔት ቤቱ << ለምን ብዬ ?>> አልኩት አይ በቃ ውርስ አለህ ማለት ነው። ብሎ ተሳለቀብኝ

<<አረ ወዳጄ እንኳን ውርስ ስራም የለኝም>> የኔ መልስ ነበር……… <<እና እንዴት መሄድ አትፈልግም? >>አለኝ <<አዎ አልፈልግም ሀገሬን በችግሯ ሰዐት ለማን ጥዬ>> አልኩት የዛኔ እኔ ለራሴ እራሴን እንደ ብዙ ብርጌድ ጦር የተመለከትኩት ስለመሰለኝ ዝም አልኩ።

በዚህ መሀል የአንደኛው ተራ ደረሰ እና አድራሻ መሙላት ጀመረ። ትንሽ ጥያቄዎችን ሲጠያየቁ ሲመላለሱ ቆዩ እና በስተመጨረሻ ባለ ኢንተርኔት ቤቱ <<አድራሻ ኮልፌ ልበለው?>> የሚል ጥያቄ ሰነዘረ።

ትንሽ እንደማሰብ አድርጐ ተስተናጋጁም <<የለ የለ አራዳ አድርገው>> አለ መልካም ብሎ መሙላት ሲጀምር ከደንበኛው እኔን ያስፈገገች ከእኔ ውጪ ባለ ኢንተርኔቱ ሰውዬ እንኳን ሰምቷት ብዙም ቁብ ያልሰጣትን ጥያቄ ጠየቀ

<<አራዳ ሲባል ፒያሳን ይጨምራል?>> አለ ጉድ አልኩ ዞሬ እያየሁት


ባለ ኢንተርኔት ቤቱ ሰውዬ <<አዎ የአራዳ ልጅ>> ብሎ አለፈው ድንቄም የአራዳ ልጅ እኔ ግን አዕምሮዬ ላይ ተመላለሰ አለማወቅ አይሉት ፒያሳን ከአራዳ ነጥሎ ማወቅ ፒያሳን ካለማወቅ በላይ ይከብዳል ታዲያ እንዴት?

ከዚህ ግን ያስፈገገኝ የባለ ኢንተርኔቱ መልስ ነበር። አዎ የአራዳ ልጅ ፎገረው ሰውዬው ግን በአራዳ ልጅነቱ ተመፃድቆ መቀመጫው ላይ ተመቻቸ። አረ እንደውም የአራዳ ልጅ በመሆኑ ተመፃድቆ ዞር ብሎ እኔን ገላምጦ ፋራ ያለኝም ይመስለኛል ያው በውስጡ መሰለኝ ነው ።

ታዲያ እኔ ምኔ ሞኝ እሱ ብቻማ በውስጦ ሰድቦኝ አይቀርም ብዬ እኔም ይሉሽን አልሰማሽ ገበያ ባልወጣሽ ብዬ ገላመጥኩት ያው በውስጤ።

ብዙም ሳይቆይ ሌላ አንድ ሰው መጥቶ አጠገቤ ተቀመጠ። አንድ ነገር አንስቶ መጫወት ጀመረ። <<ንግድ ባንክ ከአስረኛ ክፍል በላይ ያሉ ሰዎችን አወዳድሮ እየቀጠረ ነው ለምን አትሞክርም ?>> አለኝ።

ስራ እንደሌለኝ እንዴት እንዳወቀ ግራ ገብቶኝ ገልመጥ ገልመጥ አድርጌው አልፈልግም አልኩት።

<< ስድስት ሺህ ይከፍላሉ>> አለኝ በደሞዝ ሊያማልለኝ።

<< የለም ይቅርብኝ ምን ጐደለብኝና እሰራለሁ>> አልኩት ግራ ተጋባ መሰለኝ ዝም ብሎ ያዳምጠኝ ጀመር።

ለደሞዝ ብዬ እራሴን የማጣበትን ስራ ስለምን ብዬ እሰራለሁ። ስራ በደሞዝ አይለካም ብዬ አያሌ ክርክሮችን ስራ አለመስራቴንም በመረጃ አስደግፌ ደረደርኩለት ለመከራከር ሲሰናዳ ባለእንጀራዬ <<ተነስ እንሂድ ጨረስኩ>> አለኝ የሆነችዋ ነገር አለቀች ሰውዬው ሀሳቡን ባለመናገሩ በሽቆት አፀፋውን እየገላመጠን ወጣን።


የህንፃውን ደረጃ እየወረድን አንድ ሲቀረን አደናቀፈኝ። ባለእንጀራዬ እይዛለሁ ብሎ ፊቴን ቧጨረኝ። ብወድቅ ይሻል እንደነበር እየነገርኩት እየተሳሳቅን ታክሲ ለመያዝ አስፓልቱን ተሻግረን ቁልቅል ትንሽ ወረድን።

ከብዙ አሰልቺ ጥበቃ ቡሀላ አንድ ባዶ ታክሲ መጥቶ እንደ ማነኛውም አዲስ አበቤ ተጋፍተን ገባን።

ገብተን ከኋላ ወንበር ተቀመጥን ሙሉ ነገሬ እንደገባ እያረጋገጥኩ ሌላ አንድ ከሀሳብ የገዘፈች ሴት መጥታ ሁለት ሰው የሚይዘውን ወንበር ሞላችው። የጉድ ሀገር ብዬ ዞር ስል አንድ ለግላጋ ወጣት ታክሲው ሞልቶበት ብቻውን ቅጭም ቅጭም እያለ ቆሟል።

<< አረ አስገቡት አራተኛ ሰው>> አልኩ ብርዱ እኛን ሰቆጣ ሲያስጨፍረን ስለቆየ የእሱም እጣ ፈንታ እንዳይሆን ብዬ………


ሁሉም ዝም <<አረ ይበቃናል አስገቡት ዝም………… በዚህ ብርድ አያሳዝንም በእናታችሁ አስገቡት>> ስል አጠገቤ የተቀመጠችው ሴትና ከፊት ለፊቷ ያለችው የእርሷ ቢጤ ሴት ጋር ተመሳጥረው <<ምነው ወንድምህ ነው እንዴ>> ብለው ከሩቅ ሊሰማ የሚችል አይነት ሳቅ ሳቁብኝ………

እስኪጨርሱ ዝም ብዬ ተመለከትኳቸውና አንድ ቃል ብቻ እንዲሰሙ አድርጌ ተናገርኩ "መተዛዘን አሳቀ?" አልኩ በጥያቄ መልኩ የሳቃቸው ፍም ላይ ውሀ ተቸለሰበት ዝም አሉ ።

ከዚህ በኋላ ያለውን ይስሙኝ አይስሙኝ ባላውቅም…… ለነገሩ እናንተ ምን አጠፋችሁ መተዛዘን መደጋገፍ ቅንጦት ሆኗል አንዱ ለአንዱ የሚያዝነው የስጋ ወንድሙ ወይ የእሱ ዘር ከሆነ እሱም እድለኛ ከሆነ ነው ። እነዚህን የመሳሰሉትን ግማሹን በውስጤ ግማሹን በአንደበቴ እየተናገርኩ ታክሲው ገሰገሰ። ባለእንጀራዬ ተናደድ እንጂ በደንብ …………በቃ ይህችን ብቻ ነው የምትናደድ………… አለመናደድህ እኔን አናደደኝ………… እያለ ይነዘንዘኛል የሁል ጊዜ ማፅናኛው እንደሆነ ስለማውቅ በእሱ ድርጊት ንዴቴን ዘንጋ አደረግኩና ወደማይመለከተኝ እርዕስ አዘነበልኩከፊታችን ያለው ወንበር መደገፊያው የተገነጠለ
368 views15:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-12 18:48:06 ትልቅ እና ትንሽ



ካሊድ(ሀበሺስታን)




የሰው ትልቅነቱ የትኛው ነው? እድሜው፣ኑሮው፣የአካሉ ግዝፈት፣የሰውነት ልዕልናው ፣ወይስ የማሰብ አቅሙ? ትልቅ ለመባል ሰው ምን ምንድን መስፈርትስ ማሟላት አለበት?
እከሌ ትልቅ ሰው ነው እከሊት ትልቅ ሴት ናት ሲባል ምን ለማለት ተፈልጐ ነው?


አንድ አንድ ሰው አለ ለመከበር የሚመች ትልቅ ነኝ ሳይል ወደን ፈቅደን ትልቅ እንደሆነ እንድንመሰክር የሚያደርግ ሰዋሰዋዊነት ያለው የፊቱ ፀዳል የአነጋገር ዘየው እንዲሁ ጠምዝዞ ትልቅ ሰው ነው የሚያስብለን።


ሌላውም አለ ትልቅ ነኝ ባይ ትልቅነቱን ለማስመስከር ከአፉ ቃል ሲወጣ ትንሽነቱ ቀድሞ ተንደርድሮ ብቅ የሚልበት።


ትልቅነት በእድሜ የሚመስለውም አለ። እርግጥ ነው "እድሜውን የመሰለ የእድሜ ባለ ፀጋ እውነትም ትልቅ ነው" ግና ሰው እድሜውን ካልመሰለ መበላሸቱ እርግጥ ነው።
"ሰው እድሜውን ከመሰለ እድሜ ጌጥ ነው የፈጣሪ በረከት"።

በእድሜ ትልቅ ነኝ የሚል ሰው በእድሜ ለሚያንሰው ለታናሹ ስራ ያዝዛል በእድሜ ትንሹም የለም አሻፈረኝ አልታዘዝም ይላል ታዲያ የዚህ ጊዜ በእድሜ ትንሹን መቆጣት አልፎም መቅጣት ይቀድማል ወይስ በእድሜ ትልቁ በእድሜ ትንሹ ለምን እምቢኝ አለ ብሎ ማሰብ እራስን መመርመር ይቀድማል? ምን አልባት ለትንሹ ለትልቅ እንዴት እንደሚኮን አላሳየው ይሆናል ትልቁም ለትንሹ መጀመሪያ ከማዘዙ በስተ ፊት ምን መሆን እንዳለበት አልገባው ይሆናል። እድሜ ትልቅነትን አያሳይም ስንት የትልቅ ትንሽ አለ ? ስንት ልጁ የሚበልጠው አባት አለ? ስንት ትንሹ የሚበልጠው ትልቅ ወንድም ትልቅ እህት አሉ?ቤቱ ይቁጠረው


አንድ አባባል አለ "ከእድሜ ባለፀጋዎች ተጠጋ እውቀታቸውን ቅሰም ምክንያቱም ከመፅሀፍት ያላገኘኸውን እውቀት እነሱ ዘንድ ታገኘዋለህ"ይላል እውነት ነው ትልቅነት ትልቅ ለመሆን መንደርደር ያሉበትን ትንሽነት ማወቅ ነው። ተጨባጩን ቁጭ ብሎ ያሰላሰለ ለማስተካከል መዳፉን ያዘጋጀ አዕምሮውን የሞረደ እግሩን ያነሳ መንገዱን የጀመረ በእርግጥም ትልቁ እሱ ነው ለመለወጥ ከተነሳ በላይ ትልቅ የለም ትልቅነት የሚጀምረው ትንሽነትን ከውስጥ ፈልጐ በማግኘት ነው ትልቅነት ከሜዳ አይገኝም ትልቅ ሳይሆኑ ትልቅ ለመምሰል ከመሞከር ትንሽነትን ማወቅ መንገዱን ቀና ያደርገዋል "ትልቅ ለመምሰል ከመሞከር በላይ ትንሽነት የለም"።


ትልቅነትን እና ትንሽነትን ካልኳቸው ሁሉ በላይ አንድ የሚገልፅልኝ ነገር አለ………



ፈጣሪ በጣም ሲያተልቅ በጣም ሲያከብርህ ትልቅነትን በምድር ላይ ሲመሰክርልህ ሲያውጅልህ እንዲህ ያደርጋል……… ልክ እንደ ሴት እህት እንደምትሆነዋ ሚስት እንደምትሆነዋ እናት እንደምትሆነዋ ድንቅ ፍጥረት በጣም ያከበራትን የስንት ተጋድሎ የስንት በጐ ምግባር ውጤት የምትሆነዋን በጣም በውድ እንጂ የማትገኘዋን ውስጧ ምንም እንከን የሌለባትን ውድ በረከት የሆነችዋን ጀነትን ከእግርህ ስር ያደርግልሀል………… ይህ ነው ትልቅነት የአለም ሀያል መሆን ይህ ነው ይህ ትልቅነት በፈጣሪህ ሲታወጅልህ ደግሞ ትልቅነት ወደር ያጣል።


ከነዚህ በጣም የሚያሳፍረው ግን ትልቅን ነገር ትልቅነትን ከእግር ስር አኑሮላት እረግጣ የሄደች ሴት ነኝ ባይ ሴት ዋ ለሷ!!!



@Habeshistan
441 viewsedited  15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-06 18:57:18 የመፃተኛ እንጉርጉሮ

ያኔ ዋዛ ሳለ፤ ግድግዳ፤ጣራ፤በር
ዞሮ ዞሮ ከቤት፤ይሉት ፈሊጥ ነበር
ለንስር ጎጆ አለው፤ በሬም አለው በረት፤
የኔናንቺ ድርሻ፤
ቤት ጎምዥቶ መቅረት፤
አገር ናፍቆ መቅረት፤
መንገድ አቅፎ መቅረት፤
ዞሮ፤ዞሮ፤ዞሮ፤ እንደገና ዙረት፡፡
362 views15:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-01 19:25:30 ✦ አመድ መልሶ የሚበተነው ወደበተነው ሰው ፊት ነው፡፡ ( ናይጄሪያውያን)
452 views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-01 19:23:59 ✦ ሁሉም ያነበብከው ትክክል ነው ብለህ የምታምን ከሆነ ባታነብ ይሻላል። ( የጃፓንያዊያን አባባል )
417 views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-01 19:22:27 ✦ አባቴ ሲሞት እወርሳለሁ ያለና ለሚመጣው ክረምት አርሳለሁ ያለ ሁለቱም ከድህነት አይወጡም፡፡ ( ኢትዮጵያውያን አባባል)
403 views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-28 21:04:32 የተከበራችሁ እራሳችሁን ያከበራችሁ ያስከበራችሁ የሀበሻዊ ጥበባት ተከታዮች የአንችን ብዬ ተከታታይ ልብ ወለድ አንባቢያን የነበረን የስድስት ምዕራፍ የ56 ክፍል የንባብ ቆይታ ብዙ አንስተን ብዙ ጥለናል ብዙ ነገር ውስጥ ገብተን ወትተናል ከኑሬ ጋር ድሬ ደዋ ከሀበሽ ጋር በሀሳብ ነጉደናል ከመሲ ጋር ካፌ ተሰይመናል ብዙ አይተናል።


ለነበረን ቆይታ እጅጉን ምስጋናዬን ልቸራችሁ እፈልጋለሁ። በካራክተሮች ላይ የነበራችሁን ቁርኝት በማለቁ የተሰማችሁን እንኳን አለቀም የምትሉ ለምን አለቀም ለምትሉም ለወቀሳም ለሙገሳም ወይም ከዚህ በኋላ እንደዚህ አይነት ታሪክ ብትፅፍልን ለማለት……… @Habeshistann አድራሻዬ ነው። አመሰግናለሁ።ፀሀፊ ካሊድ(Habeshistan)


በሌላ ፅሁፍ እስከምንገናኝ በሌላ አጫጭር ፅሁፎች ግጥሞች አብረን የምንቆይ ይሆናል።
429 viewsedited  18:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ