Get Mystery Box with random crypto!

የጉመር ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

የቴሌግራም ቻናል አርማ gummerw — የጉመር ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት
የቴሌግራም ቻናል አርማ gummerw — የጉመር ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት
የሰርጥ አድራሻ: @gummerw
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 733
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችና ጥቆማዎች ለማድረስ
251113110443
የስልክ ቁጥራችን ላይ ልታደርሱን ትችላላችሁ!!!
ትክክልኛ መረጃ ለህዝቡ እናድርስ!!!
የጉመር ወረዳ መንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-15 10:19:59 አጠቃላይ በነበረው ሂደት 142 ክስ የተመሰረተባቸው ሰዎች ላይ የፌዴራል አቃቤ ህግ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አርባ ምንጭና አካባቢው በሚያስችለው ችሎት ላይ ክስ መስርቷል፤ ተጠርጣሪዎቹ ካሉበት ቦታ ወደዚያ ተዛውረው ክሳቸውን የሚከታተሉ ይሆናል፡፡ በአጠቃላይ በዚህ አካባቢ ከተከሰተው ግጭት ጋር ተያይዞ 247 ሚሊዮን ብር የዋጋ ግምት ያለው ንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

ሚያዚያ 18 /2014 ዓ.ም በተፈጥሮ ሞት የሞቱትን ታላቅ የእምነት አባት ሸክ ከማል ለጋስ የቀብር ስርዓታቸውን ለመፈጸም በጎንደር ከተማ ቀበሌ 8 አካባቢ በሚገኘው ወደ ሀጅ ኤልያስ መካነ መቃብር የእስልምና እምነት ተከታዮች መካነ መቃብር ወደ ሆነው አስከሬናቸውን ለማኖር ወዳጅ ዘመዶቻቸው ወደ ቦታው በሄዱበት ከቀኑ 7ሰዓት30 ላይ በተለምዶ ቀሀ ወንዝ ከሚባለው ድንጋይ በማውጣ መቃብሩን ለማመቻቸት በሚደረግ ሂደት ውስጥ አስቀድሞ በአጎራባችነት የነበረ የኦርቶዶክስ አማኞች የሚያመልኩበት አበራ ጊዮርጊስ የሚባል ቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ የአብነት ተማሪዎች ከዚያ በፊት የድንበር ችግር በመኖሩ ድንጋዩን የሚወስዱት ድንበር ሊያካልሉ ነው በሚል ድንጋይ መወራወር ይጀምራሉ፤ በዚህ ሂደት አንደኛ ተከሳሽ የሆነው የቤተክርስቲያኑ ጥበቃ ጥይት ወደ ህዝቡ በመተኮስ ቦንብ እንዲወረወር በማድረጉ ምክንያት በዚያን ቅጽበት ብቻ ሶስት ሰዎች ሂይወታቸው አልፋል ብለዋል፡፡
ግጭቱ ተስፋፍቶ ወደ ከተማው በመሰራጨቱ በተከታታይ ቀናት የተለያዩ ግጭቶች መኖራቸውን የምርመራ መዝገባችን ያስረዳል ያሉት አቶ ፍቃዱ መጀመሪያ የጸጥታ ሀይሉ 509 ሰዎችን በቁጥጥር ስር አውሎ 310 ወንጀል ውስጥ መሳተፋቸውን የሚያሳይ ማስረጃ ባለመገኘቱ ወዲያው እንደተለቀቁ ተናግረዋል፡፡

199 ቀድመው የተያዙና 17 ከዚያ በኋላ የተያዙ ሰዎችን አንድ ላይ በማድረግ በ216 ሰዎች ላይ የጊዜ ቀጠሮ እየተጠየቀ በአጭር ጊዜ ውስጥ 121ቹ ወንጀል ስለመፈጸማቸው ማስረጃ ባለመኖሩ እንዲለቀቁ ተደርጎ በአጠቃላይ 77 የተያዙ፣ 62 ያልተያዙ ሰዎች ላይ ምርመራ ሲጣራ ቆይቷል፡፡ መጨረሻ 250 የሰው ምስክሮች ከተሰበሰበቡ በኋላ በፍርድ ቤት ክስ ሊያስመሰርትባቸው በሚችል 103 ሰዎች ከሁለቱም ዕምነቶች ተለይተው ክስ ተመስርቶባቸዋል፤ 69 ተይዘው የታሰሩ 34 ደግሞ ተፈላጊዎች ሲሆኑ 24 የዕስልምና እምነት ተከታዮች፤ 79 ደግሞ የክርስትና ዕምነት ተከታዮች ናቸው፤ ከእነዚህም ውስጥ 3ቱ ሴቶች መሆናቸውን አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡

ግጭቱ ባህሪው ቀድሞ ታስቦበት ያልነበረ በቀብር ስነ-ስርዓቱ ላይ የተፈጠረ ነገር ግን የሰፋ፤ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች የእስልምና ዕምነት ተከታዮችን የማምለኪያ ቦታ እና የንግድ እንዲሁም የመኖሪያ ቤቶችን በመምረጥ ጉዳት በማድረስ፤ የእስልምና ዕምነት ተከታዮችም ደግሞ አጸፋው የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች የንግድ ቦታ ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን የምርመራ ግኝታችን ያመለካክታልም ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታው፡፡
አያይዘውም 20 ሰዎች ከሁለቱም ዕምነት በግጭቱ ለሞት ተዳርገዋል፣ ከ100 ሰዎች በላይ የአካል ጉዳት ደርሷል፣ 60 ሚሊዮን ግምት ያለው ንብረት ውድሟል፤ የዕስልምና ዕምነት ተከታች በዕምነቱ በኩል ያቋቋሟቸው ኮሚቴዎች ደግሞ ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳት ደርሷል ብሎ ያመጣ ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ በኩል ግን 60 ሚሊዮን የሚል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በስልጤ ዞን ከተፈጸመው ወንጀል ጋር በተያያዘ ወራቤ ሳንቁራ ወረዳ በአለም ገበያ ከተማና መንዝር ጦር በርበሬ ወረዳ በተባሉ አካባቢዎች የተፈጸመ ወንጀል በሚያዝያ 18 2ዐ14 ዓ.ም. ጎንደር የተከሰተውን ወንጀል ተከትሎ ማታ 2፡00 ሰዓት ከሰላት በኋላ አንድ አሰጋጅ እና አንድ ኡስታዝ ጎንደር የፈሰሰው ደም የናንተ ደም ነው፤ ጎንደር ሙስሊሙን የገደለው ክርስቲያን ነው ስለዚህ እንዲኖሩ መፍቀድ የለብንም ብለው የቀሰቀሱ በመሆኑ በማግስቱም ከቀኑ7፡00 ሰዓት ላይ በነበረው ሰላት ተመሳሳይ ቅስቀሳ በማድረጋቸው በትምህርት ቤቶችም በመቀስቀስ መስጊድ ተቃጥሏል ብሎ በማስወራት ወደ ብጥብጥ እንዲገቡ ተደርጓል፡፡

በወራቤ ከተማ ቅዱስ ሩፋኤል በተባለ ቤተክርስቲያን ላይ ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ በመሄድ ቤንዚል እና የተለያዩ ስለታማ ነገሮችን በመያዝ ውድመት መጀመራቸውን የወራቤ ዩኒቭርስቲ የኦርቶዶክስ ዕምነት ተከታዮች ቤተክርስቲያናችን ተቃጠለ ብለው በመምጣታቸው ብጥብጡ መባባሱን በአካባቢው ባለው መስጊድም ሊቃጠል ነው የሚል የአዛን ድምጽ በማሰማት የሰው ቁጥር እንዲመጣ ተደርጎ ቤተክርስቲያኑ መቃጠሉን የምርመራ መዝገቡ ያሳያል፡፡
ከላይ በተጠቀሱት ሌሎች ወረዳዎችም ጭምር 4 የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ቤተክርስቲያን ንዋየ ቅዱሳትን ጨምሮ እንዲሁም 3 የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያናት መቃጠላቸውን እንዲሁም የዋጋ ግምቱ ወደ 46 ሚሊዮን ብር የሚጠጋ ንብረት መውደሙን የምርመራ ግኝቱ ያመላክታል፡፡
ሚኒስትር ዴዔታው እንደገለጹት ከሆነም የምርመራ መዛግብቱን መሰረት በማድረግ በ97 ሰዎች ላይ ክስ ተመስርቷል፡፡

በመጨረሻም ሚኒስቴር ዴኤታው በሁሉም ግጭት በተፈጸመባቸው ቦታዎች ውስጥ የጸጥታ መዋቀሩ ገብቶ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አንስተው፤ በቅርቡ በወለጋ ግንቢ አካባቢ የተፈጸመው ወንጀልን ጨምሮ መቻሬን እና ጋንቤላ የተፈጸመው ወንጀል ላይ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ተናግረው፤ ወንጀል ሀይማኖትንና ብሄርን የማይወክል መሆኑን በመገንዘብ በየደረጃ ያለው የመንግስት አደረጃጀትና ህብረተሰብ ትብብር ሊያደርግ ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡


https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0uvYmij9VMGPpdDDjuhqWtQCm6xmgLAYLggG2yzQRu7vFpkYCze9YvEFH37mipFZUl&id=100068870753847
144 views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 10:19:59 ሐምሌ 8/2014 ዓ.ም

በጎንደር፣ በወራቤ እና በጂንካ በተከሰተው ግጭት የተፈፀሙ ወንጀሎች የምርመራ ግኝት ይፋ ተደርጓል።

ከፍትህ ሚኒስቴር የተገኘው ምሉ መረጃ:
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር በመተባበር በሚያዚያ ወር በጎንደር፣ በወራቤና በጂንካ አካባቢ በተከሰተው ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎችን የምርመራ ግኝት ይፋ አደረገ፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴር ከፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ ጋር በመተባበር በሚያዚያ ወር በጎንደር እና በወራቤ ሀይማኖትን መሰረት አድርጎ እንዲሁም በጂንካና አካባቢው ማንነትን መሰረት አድርጎ በተከሰተው ግጭት የተፈጸሙ ወንጀሎችን የምርመራ ግኝት ይፋ አደረገ፡፡

የምርመራ ግኝቱን በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትህ ሚኒስቴ የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ፍቃዱ ጸጋ እና በፌዴራል ፖሊስ በወንጀል ምርመራ ጠቅላይ መምሪያ የወንጀል ምርመራ ኦፕሬሽን መምሪያ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሙልኢሳ አብዲሳ በጋራ በመሆን ለሚዲያዎች አብራርተዋል፡፡

በጎንደር ሚያዝያ 18/2014 ዓ.ም በአንድ የእስልምና ኃይማኖት አባት ስርዓተ-ቀብር ላይ ለቀብር የሚሆን ድንጋይን ሰበብ በማድረግ በተከሰተው ግጭት በ20 ሰዎች ላይ ሞት፣ በ100 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንዲሁም በ1 መስጊድ ላይ ሙሉ በሙሉ ውድመት እና በ8 መስጊዶች ላይ ከባድ ጉዳት እንዲሁም በ2 መስጊዶች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን አቶ ሙልኢሳ አብራርተዋል፡፡

አቶ ሙሊሳ በማብራሪያቸው ፖሊስ የ250 ሰዎችን የምስክርነት ቃል ተቀብሏል፤ ሌሎች ከወንጀል አፈጻተሙን የሚያስረዱ የተለያዩ ማስረጃዎችን አሰባስቧል፡፡ በዚሁም መሰረትም 509 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በወንጀል ድርጊቱ የተሳተፉ ሰዎችን የመለየት ሥራ ተሰርቷል፡፡ በዚህም መሰረት የተደራጀውን የምርመራ መዝገብ ለዐቃቤ ሕግ አስረክበናል ያሉ ሲሆን ዐቃቤ ሕግም የክስ መመስረት ሂደቱን ጀምሯል ብለዋል፡፡

በስልጤ ዞን ወራቤ ከተማ ጎንደር የተፈጸመውን የሀይማኖት ግጭት መነሻ በማድረግ ወንጀሉን ከህዝብ ጋር ሆኖ ከመከላከል ይልቅ፤ አንዳንድ ጽንፈኛ ኃይሎች በጎንደር መስጊድ ተቃጥሏል ውጡና የክርስቲያን ቤቶችን አቃጥሉ በማለት በከተማው ማይክራፎን ይዘው በመቀስቀስ በ4 የኦርቶዶክስ እንዲሁም በ3 የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያኖች ላይ ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉ ሲሆን፤ ጉዳት አድራሾቹ የሞተር ሳይክልና ገጀራዎችን በመጠቀም በ2 ሰዎች ላይ ሞት፣ በ79 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት እንዲሁም 12 በሚሆኑ በግለሰብና በንግድ ቤቶች ላይ ከባድ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል ሲሉ አቶ ሙልኢሳ በመግለጫቸው አመላክተዋል፡፡

ጂንካ ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘም የአሪ ብሄረሰብ ዞን እንሁን በሚል የከተማውን ከንቲባ ጨምሮ ሻንካ /ወጣት/ የሚል ቡድን በማደራጀት ቅስቀሳ በማድረግ ማንነትን መሰረት ያደረገ ጥቃት በአማራ ተወላጆች ላይ ፈጸመዋል ያሉት አቶ መልኢሳ፤ በተጨማሪም 247 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ደርሷል፤ 1150 የሚሆኑ ሰዎች ደግሞ ከመኖሪያ ቀያቸው ተፈናቅለዋል ብለዋል፡፡
አቶ ሙልኢሳ አክለውም የህግ ማስከበር ሂደቱን የፌዴራል ፖሊስ ከፍትህ ሚኒስቴር ጋር በመሆን እንደሚቀጥል ተናግረው፤ ህብረተሰቡም ወንጀል ፈጻሚዎችን ከመደበቅ ይልቅ በማጋለጥ ወንጀልን በመከላከሉ ረገድ ከህግ አካላት ጋር በመሆን በጋራ እንዲሰራ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የክስ ሂደቶችን እና ጥልቅ የሆኑ የምርመራ ስራዎችን በተመለከተም በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ሚኒስቴር ዴኤታ የሆኑት አቶ ፍቃዱ ጸጋ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በጂንካ ማንነትን መሰረት ያደረገው ጥቃት ሚያዚያ 1 ቀን መፈጸሙን አውስተው፤ ነገር ግን ጉዳዩ ከመጋቢት ወር ጀምሮ ዝግጅት ሲደረግበት መቆየቱን የምርመራ ግኝቱ እንደሚያመላክት ተናግረዋል፡፡
ሚኒስቴር ዴኤታው አክለውም በደቡብ ኦሞ ዞን የተፈጸመው የወንጀል ምርመራ መሰረት የሚያደርገው ጂንካና አራት የአሪ ብሄረሰብ ተወላጆች የሚኖሩባቸው ወረዳዎች ላይ የተፈጠረውን ግጭት መሆኑን አንስተዋል፡፡

በአሪኛ ሸከን ወይም ወጣት ተብሎ የተደራጀ ቡድን፤ በደቡብ ኦሞ ዞን ከሚኖሩ 16 የተለያዩ ብሄር ብሄረሰቦች ውስጥ እኛ ለብቻችን የጂንካን ከተማን ጨምሮ አራት ወረዳዎችን በመያዝ ዞን መሆን አለብን፤ የሚል ዓላማን በማንገብ ኢ-መደበኛ አደረጃጀት በመፍጠር በወረዳውም በዞኑም ያሉ የመንግስት ኃላፊዎች ጭምር ያደራጇቸው ወጣቶች፤ የዞን ጥያቄያችን የማይቀበለው የአማራ ብሄር ተወላጅ ነው ስለዚህ በመጀመሪያ የአማራ ተወላጅን ነው ከአካባቢው ማስወጣት ያለብን የሚል ይዘት ያለው ቅስቀሳ አድርገዋል ሲሉ አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል፡፡
በተለይም ከመጋቢት 26/2014 ዓ.ም ጀምሮ የኑሮ ውድነትን ሰበብ በማድረግ የአማራ ነጋዴዎችን ሱቅና ቤት በመበርበር ተለያዩ ዕቃዎችን ወደ ማዘጋጃ ቤት ወስዶ በማከማቸት ሂደት ላይ ከቆዩ በኋላ በተለይ በወረዳዎች ላይ ሚያዚያ 21/2014 ዓ.ም የሸከር ዋነኛ አደራጅ የነበረው አቶ ማቲያስ በአማረው ተገድሏል በማለት ወሬ በማናፈስ በጂንካ ደግሞ ሰልፍ እንዲኖር በማድረግ አስቀድመው በለዩት የአማራ ተወላጆች ቤት ላይ ጥቃቶች መፈጸማቸውን የምርመራ ግኝታችን ያመላክታል ብለዋል፡፡
በዚህ ጊዜ ወደ 144 የአማራ ተወላጆች ቤት ሙሉ በሙሉ ተቃጥለዋል 46 ቤቶች በድንጋይና በተለያዩ ቁሳቁሶች ጉዳት እንዲደርስባቸው መደረጉንም የገለጹት ሚኒስቴር ዴኤታው በተጨማሪም አንድ መስጊድ ተቃጥሏል፣ 232 የንግድ ድርጅቶች ተዘርፈዋል ጥቃቶቹም የተፈጸሙት በአማራ ብሄር ተወላጆችና በሌሎች የእነሱን መደራጀት አይደግፉም ያሏቸው ብሄሮች ላይ ነው ብለዋል፡፡

በሂደቱ 782 ተጠርጣሪዎችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ያዋለ ሲሆን ከ782 ተጠርጣሪዎች ውስጥ በፌዴራል መንግስቱ ስልጣን ስር ይወድቃሉ የተባሉ 142 ተከሳሾች ላይ በፍትህ ሚኒስቴር በጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ዘርፍ ክስ ተመስርቶባቸዋለው፤ ሌሎቹ በዞን በወረዳ እንደየስልጣናቸው ክስ እንዲመሰረትባቸው መደረጉንም አቶ ፍቃዱ በመግለጫቸው አብራርተዋል፡፡
በወንጀሉም ላይ የጂንካ ማዘጋጃ ቤት ኃላፊ፣ የጂንካ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የጂንካ ከተማ ፋይናንስ ጽ/ቤት ኃላፊ፣ የደቡብ አሪ ወረዳ አስተዳደር፣ የጂንካ ዩኒቨርስቲ መምህርና የተለያዩ የመንግስት ሰራተኞች የተሳተፉበት ከመንግስት ፋይናንስ እየወጣ ለወጣቶቹ አበል በተለያየ መንገድ የተከፈለበት ሂደት እንደነበር የምርመራ ግኝታችን ያሳያል ብለዋል፡፡
ምርመራው በደረሰበት ልክም የመንግስት አስተዳደር ላይ ያሉ ሰዎች በወንጀሉ ውስጥ በመሳተፍ ትልቅ ሚና እንደነበራቸው ተረጋግጧል ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታው እስከዛሬ ከመረመርናቸው በተለየ ከ8 ሰዎች ውጭ ሌሎቹ በቁጥጥር ስር ውለዋል፤ በተጨማሪም ምንም የሰው ህይወት ሳይጠፋ 8 ሰዎች ላይ ብቻ የተለያያ ጉዳት ደርሷል፡፡ መከላከያ፣ የፌዴራል ፖሊስና ልዩ ኃይል በቶሎ መግባታቸው ከዚህ የከፋ ጉዳት እንዳይደርስ እንድንከላከልም አግዞናል፤ ያሉት ሚኒስቴር ዴኤታው ይህ ጉዳት የደረሰውም አንዳንድ ወረዳዎች ላይ ከአቅማችን በላይ የሆነ ነገር የለም በሚል አመራሮቹ በወንጀሉ ላይ በመሳተፋቸው የጸጥታ አካላት እንዳይገቡ በማድረጋቸው ነው ብለዋል፡፡
133 views07:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 08:14:43 የበቆሎ የጤና ጥቅሞች

በቆሎ መመገብ ከመደበኛ የምግብነት ጥቅሙ ባሻገር በርካታ ትሩፋቶች እንዳሉት የጤና እና የሥነ-ምግብ ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡

በቆሎ በአሰር (ፋይበር) የበለፀገ በመሆኑ በቆሎን መመገብ ለሆድ ድርቀት እና ተያይዞ ሊከሰት ከሚችለው የኪንታሮት ሕመም እንዲሁም የፊንጢጣ ካንሰር የመጋለጥ ዕድልን እንደሚቀንስ ተጠቁሟል፡፡

በቆሎ ለአጥንት ጥንካሬና ዕድገት ብሎም ለልብ ጤና ጠቀሜታ ያላቸውን ፎስፈረስ እና ማግኒዢየም የተባሉ ንጥረ-ነገሮችን በበቂ መጠን እንደያዘም የሥነ-ምግብ እና ጤና ባለሙያዎች ይጠቅሳሉ፡፡

በቆሎ መመገብ የማይመከረውን የኮሌስትሮል ዓይነት ለመቀነስ እንደሚረዳ እና ከፍተኛ የኮሌስትሮል መጠንን ተከትሎ በሚመጡ ሕመሞች እንዳንጠቃ እንደሚያደርግም ተነግሯል፡፡

በቆሎ በቫይታሚን ቢ በተለይም በታያሚን የበለፀገ በመሆኑ ለነርቭ ጤና ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት ተገልጿል፡፡

በቆሎ የ“አንቲኦክሲደንት” ባህሪ ስላለውም ካንሰርን የመከላከል አቅም እንዳለው የጤና ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በቆሎን መመገብ ለዓይን ጤና፣ የደም የስኳር መጠን ለመቆጣጠር፣ አኒሚያን “ ደም ማነስን ” ለማከም፣ እንዲሁም ለሰውነታችን አስፈላጊ የሆኑ “አሚኖ አሲዶችን” ለማግኘት እና አመጋገባችንን ከ”ግሉተን”-ነጻ ለማድረግ ይመከራልም ተብሏል።

100 ግራም የተቀቀለ ቢጫ በቆሎ በውስጡ፥ 96 ካሎሪ፣ 73 በመቶ ውሃ፣ 3 ነጥብ 4 ግራም ፕሮቲን፣ 21 ግራም ካርቦሃይድሬት፣ 4 ነጥብ 5 ግራም ስኳር፣ 2 ነጥብ 4 ግራም አሰር (ፋይበር) እንዲሁም 1 ነጥብ 5 ግራም ቅባት እንደሚይዝ ኸልዝ ላይን አስነብቧል፡፡

https://www.facebook.com/100068870753847/posts/pfbid02qmC8pNeJP9BdctDSCSrWELCU3eLWkCVfnjPct69wiLzRiPaPKF9AbdBZx45Qz69tl/?app=fbl
163 views05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 17:53:22 ሀምሌ 06/2014 ዓ.ም

በአበጃይ ትምህርት ቤት ከ10 ሺህ በላይ ችግኞች ተተከለ

ጄዛንዳ የልማትና የአንድነት ማህበር 10 ሺህ የተለያዩ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች በአበጃይ ትምህርት ቤት ተክሏል።

ማህበሩ 3ተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራና የልማት ፕሮግራሙ የወረዳው ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች÷ የማህበሩ ዋናና ምክትል ሰብሳቢዎች እንዲሁም የማህበሩ የከተማና የገጠር አባላት በተገኙበት በአበጃይ ሁለተኛ ትምህርት ቤት አካሂዷል።

የጄዛንዳ የልማትና የአንድነት ማህበር ሰብሰቢ አቶ መሀመድ ውድማ እንደገለፁት ማህበሩ ከዚህ በፊት ትምህርት ቤቱ ላይ ተምረው ባለፉ ተማሪዎች የተቋቋመ መሆኑን ገልጸዋል።

ማህበሩ የልማት ስራው መስራቾቹ ባሉበት በአበጃይና በአካባቢዋ የጀመረ ቢሆንም ኢትዮጵያዊና ድንበሯ ለማዳረስ አላማ አድርጎ እየሰራ ይገኛል።

አቶ መሀመድ አክለውም ማህበሩ ዛሬ ባካሄደው 3ተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 10 ሺህ ችግኞች የተተከሉ ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ የምግብ፣ የውበትና የገቢ ምንጭ የሚሆኑ ችግኞች መሆናቸውን አብራርተዋል።

ማህበሩ ለአይደራ፣ ለአሰለጫ፣ ለእንጀፎ፣ ለአበጃይ አንደኛና ሁለተኛ፣ ለሰነን ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያንና ለጉርአምባ መስጂድ የውበት ችግኞች በስጦታ አበርክቷል።

ከዚህ በተጨማሪም በወረዳው በአረቅጥ ከተማ በሆቴሉ ዘርፍ ተሰማርቶ ለህብተረሰቡ አገልግሎት እየሰጠ ለሚገኘው ግጥም ካፌም የውበት ችግኞችና ልበ ወለድ መፅሐፍቶች በስጦታ ማበርከታቸውን ሰብሳቢው ተናግረዋል።

ከልማትና ከአረንጓዴ አሻራ ስራው ጎን ለጎን 220 ሺህ ብር ወጪ በማድረግ በወረዳው ከአይደራ፣ ከአሰለጫ፣ ከእንጀፎ፣ ከአበጃይ አንደኛና ሁለተኛ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡና ከየትምህርት ቤታቸው ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የቦርሳና የማጣቀሻ መፅሐፍት ድጋፍ በማድረግ ተማሪዎቹን አበረታቷል።

በፕሮግራሙ የተገኙት የጉመር ወረዳ ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደገሙ አለሙ በበኩላቸው÷ ማህበሩ ለትውልድ የሚተላለፍ ልማቶች ለይቶ ወደ ስራ መግባቱ የሚበረታታና በቀጣይም ለበለጠ ስራ የሚያደርስ መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ የወረዳው መንግስት የማህበሩ ጋር በመሆን በማህበሩ የተጀመሩ በጎ ጅማሮዎች ለማስቀጠል በቅንጅት እንሰራለን ብለዋል ሲል የዘገበው የጉመር ወረዳ የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

- ኢትዮጵያን እናልማ!
- የፈረሰውን እንገንባ!
- ለፈተና እንዘጋጅ!!


https://www.facebook.com/100068870753847/posts/pfbid0dqEnqVYRfbnLKmQHd6WUhe2b68WSm479nrSsExdXs1gPFXdXPymTc2aVt6W6AEEUl/?app=fbl
172 views14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 09:50:35 ጀፎረ

በጉራጌ ባህል ጀፎረ/አውራ መንገድ/ልዩ ታሪክ አለው ለጉራጌ ጀፎረ ሁሉም ነገር ነው፡፡ አገልግሎቱም ሁለገብ ነው፡፡

ለጉራጌ መንደሮች ትልቅ ውበት መላበስ ምክንያቱ ባህላዊ የቤት አሠራሩናአሠፋፈሩ ብቻ ሳይሆን ከዘመኑ መሀንዲስ ቅየሳ የማይተናነስ በመንደሮች መሀል ለመሀል የሚያልፈው ግርማ ሞገስ የተላበሰው ባህላዊ አውራ መንገድ ነው፡፡

በጉራጌ ታሪክ ጥንት መሬት የሚከፋፈለው በባህሉ በተመረጡ አባቶች(የዥር ዳነ) የመሬት ልኬት ዳኞች አማካኝነት ስለ ነበረ ጀፎረ ልኬት ይሰጠው የነበረ ሲሆን የጎን ስፋቱ እስከ 8 zhr or 35 ሜትር ሲሆን መስቀለኛ መንገዶች በሚያልፉበት እስከ 12 zhr or 90 ሜትር ስፋት ሲኖራቸው ርዝመቱ ግን በመሀል የሚያልፍ ወንዝ ገደል ወይም ደን እስከሌለ ሳያቋርጥ ይቀጥላል፡፡

በጉራጌ ባህል ለጀፎረ (ባህላዊ አውራ መንገድ) የተቀመጠን መሬት አጥሮ ወደ ግል ግቢ መከለል በምንም መልኩ የተወገዘ ነው፡፡

በጉራጌ የጀፎረ ፋይዳው የጎላ ነው። ለአብነትም ማህበራዊ ክንውን የሚከናወኑበት÷ ሰው ሲሞት የለቅስ ስርዓት የሚከናወኑበት÷ የሰርግ ስነ ስርዓት የሚከናወንበት የሙሽራውና የሙሽሪት አጀቦች በዘፈን ግጥም የሚሞጋገዙበት÷ ህጻናት የሚቦርቁበት ጎረምሶች የገና ጨዋታ የሚጫወቱበት÷ ዳመራ የሚቃጠልበት÷ ወጣቶች ፈረስ ጉግስ የሚለማመዱበት÷ ፈረስና በቅሎ የሚገራበት÷ ኮርማዎች እርስ በርሳቸው የሚፈታተሹበት÷ የሚያጓሩበት÷ ከብቶች የሚውሉበትና የሚጠበቁበት÷ ሽማግሌዎች ስለማህበራዊ ህይወታቸውና አጠቃላይ ኑሮአቸው በጋራ የሚመክሩበት÷ ባህላዊ የዳኝነት ስርዓት የሚከናወንበት÷ መንገደኛ ያለአንዳች ችግር የሚጓዝበት ነው፡፡

ፋይዳው እጅግ በጣም ብዙ የሆነው የጉራጌ ህዝብ ባህላዊ እሴት በአለም ቅርስነት ተመዝግቦ እውቅና እንዲያገኝ ሁላችንም ልንከባከበው ይገባል፡፡

https://www.facebook.com/100068870753847/posts/pfbid0362EvoBFYvZGJa2U8EkB88DmwjMYLQN4swwheyDHWYqyeQW5on8cf9y6vX6yJx2W4l/?app=fbl
167 views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 07:45:48 በዳውሮ ዞን ማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም በጥላቻ ንግግርና በሀሰተኛ መረጃ የግል ተበዳዩን ስብዕና ያጎደፈ ተከሳሽ በእስር ተቀጣ።

በዳውሮ ዞን የታርጫ ከተማ አስተዳደር መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ሀምሌ 04/2014 የዋለው ችሎት የማህበራዊ ሚዲያ በመጠቀም በጥላቻ ንግግርና በሐሰተኛ መረጃ የግል ተበዳዩን ስብዕና ባጎደፈው ተከሳሽ በአቶ መርክነህ ማሞ ሚልካኖ ላይ የአንድ አመት ቀላል እስራት ውሳኔ አስተላልፏል።

ተከሳሹ የማህበራዊ ሚዲያ (Facebook) በመጠቀም በግል ተበዳይ ላይ ሀሰተኛ መረጃ በማሰራጨት የተበዳዩን ስም ከማጥፋትና ስብዕና ከማጉደፍም ባለፈ ግል ተበዳዩ በሚሰራበት አከባቢና መስርያ ቤት አመነታ እንዲያጣ እንዳደረገም የክስ መዝገቡ አብራርቷል።

በተከሳሹ ላይ የተላለፈው የእስር ውሳኔ የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በወጣው አዋጅ ቁጥር 1185/2012 አንቀጽ 4 እና አንቀፅ 7(ሀ) ስር የተደነገገውን አዋጅ ጥሶ በመገኘት መሆኑን የፍ/ቤት መረጃ አመላክቷል።

ይህ አይነት ወንጀል በአከባቢው የግለሰቦችን ስም በማጥፋት ግለሰቦች ተረጋግተው ስራ እንዳይሰሩ፣ ማህበረሰቡ በመንግስት ተቋማት አሰራር ላይ አመነታ እንዲያጡና እንዲሁም ግለሰቦች በሚኖሩበት አከባቢ ከማህበረሰቡ ጋር ያላቸውን መልካም ግኑኝነትን በማጥፋት በአከባቢው ሰላምና መረጋጋት እንዳይሰፍን የሚያደርግ እንደሆነ በቅጣት መዝገብ ላይ ሰፍሯል።

በመሆኑም በተመሳሳይ የወንጀል ድርጊት የተሰማራ አካል ካለ ከእንደዚህ አይነት አከባቢውንም ሆነ ግለሰቦችን ከማይጠቀም ተግባር እንዲቆጠቡ ጥሪ ያቀረበው ፍ/ቤቱ የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ሚዲያን ለልማትና ለመልካም ነገር እንዲጠቀሙ ማሳሰባቸው የዳውሮ ዞን የመንግሥት ኮምዩኒኬሽን መምሪያ ዘግቦታል።

በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
Facebook:-https://www.facebook.com/profile.php?id=100068870753847
Telegram:-https://t.me/gummerw
Youtub:-https://youtube.com/channel/UCyqat__kk7lXxzpRv8r7chA
177 viewsedited  04:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 00:24:07 በኦሬገን የአለም አትሌትክስ ሻምፒዮና ላይ አለም የሚያየው ሌላ አዲስ ፊት አለ~ አትሌት ኤርሚያስ ግርማ ከጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ

በ800 ሜትር ሀገሩን ይወክላል።

አትሌቱ ትውልዱ በጉራጌ ዞን ኧዣ ወረዳ የወንበር ቀበሌ ሲሆን በ2008 አዲስ አበባ ለትምህርት ወንድሙ ጋ ይመጣልና ከትምርቱ ጋ ስፖርት መስራትን ይጀምራል።

በኋላም ከወንድሙ ጋር በመሆን ኮልፌ ክፍለ ከተማ ሄዶ ወንዱሙ በቴኳንዶ ስፖርት እሱም በፍላጎቱ በአትሌትክስ ስፖርት ይመዘገብና ሩጫን ይጀምራል፤ በክፍለ ከተማውም በአሰልጣኝ ደምመላሽ ከበደ እየሰለጠነ ስልጠናውን ሊጨርስ የተወሰነ ጊዜ እንደቀረው የኢትዮጰያ ስፖርት አካዳሚ ማስታወቂያ ያወጣል÷ ክፍለ ከተማውም በአካዳሚው እንዲወዳደር ያስመወገበውና ይፈተናል፤

በተሰጠው የማጣሪያ ፈተናም አምስተኛ ደረጃ ቢወጣም በፈታኝ አሰልጣኞች እይታ በተለይ ደግሞ በመካከለኛ ርቀት አሰልጣኝ በሆነው በአቢዮት ተስፋዬ ግፊት በ2010 በአካዳሚው እንዲያዝ ተደረገ።

ሁሉ ነገር በተሟላበት የኢትዮጵያ ስፖርት አካዳሚም በሚገባ እየሰለጠነ አትሌቱ ከጊዜ ወደጊዜ መሻሻሎችን እያሳያ ፈጣን ለውጦችን እያሳየ የመጣ አትሌት ነው።

በአካዳሚው በአሰልጣኝ አቢዮት ተስፋዬ እየሰለጠነ በተለያዩ ውድድሮች ላይ ገና ከአካዳሚው ተመርቆ ሳይወጣ እነዚህን ፈጣን ሰዓቶች አስመዘገበ።
1:54, 1:49, 1:47 ,1:44.36

በአካዳሚው እያለ የልጁን አቅም ያዩ ክለቦች ገና ከመጀመሪያው ጀምሮ ቢያጭቱም ከአካዳሚው ተመርቆ ሳይወጣ ክለብ መያዝ ስለማይችል የክለቦች ፍላጎት ሳይሳካ ቢቀርም አትሌቱን ሲከታተል የቆየው የሲዳማ ቡና አትሌትክስ ክለብ ዘንድሮ በ2014 ሰኔ ላይ እንደተመረቀ የኔ ነህ ብሎ ወስዶታል።

አትሌቱ በአሰልጣኝ አቢዮት ተስፋዬ እየሰለጠ በግሎባል ስፖርት ማኔጅመንት ተይዞ የውድድር እድል ተዘጋጅቶለት ከላይ የተመዘገቡትን ፈጣን ሰዓቶች አስመዝግቦ ለኦሬገኑ የአለም አትሌትክስ ሻምፒዮና ላይ እና በኮሎቢያ ካሊ በሚደረገው የአለም ከ20 አመት በታች አትሌትክስ ሻምፒዮና ላይ ሀገሩን እንዲወክል ተመርጧል።

ልጁ እጅግ በጣም መልካም ስነስርዓት ያለው አትሌት ሲሆን አሯሯጡ ይመስጣል÷ እኔ ብዙ ኢትዮጵያጵያዊያን አትሌቶች ባደንቅም አሯሯጣቸው የሚስበኝ አሉ በተለይ የቀነኒሳ÷ የሲሳይ ለማ÷ የጥሩነሽ የሌሎችም የተወሰኑ አትሌቶች አሯሯጥ ያስደምመኛል÷ የዚህ ልጅ ግን ይለያል!!

ሩጫ የምትጠላ እንኳ ብትሆን ይህ ወጣት አትሌት ልጅ ሲሮጥ ካየህ በሩጫ ሰፖርት ፍቅር ትጠመዳለህ።

የልጁ አሯሯጥና ቁመና ሁሉ ነገር ስታይ ወይ የተፈጥሮ ማዳላት ትላለህ? ልጁንም ድንገት ብታገኘው እባክህ እስኪ ሩጥልኝ ትለዋለህ !!

ኳስ ሮናልዲኖህ ጎቹ እግር ላይ እንደምታምርና እንደምትሰቃይ ሁሉ ሩጫም እዚህ ልጅ ጋ ተጠቃልላ ገብታለች።

ብቻ ልጁ፣ ክለቡ፣ አሰልጣኙ እንዲሁም ማኔጅመንቱ በጋራ ተናበው ከሰሩ አትሌቱም በዚሁ ስነስርዓቱ ከቀጠለ የስፖርቱን ዲስፕሊን ካከበረ ኢትዮጵያ ሌላ ጀግና ታፈራለች።

ይህን ወጣት አትሌት በመጀመሪያ ያሰለጠነ እንዲሁም ለአካዳሚው የመለመለ ባለሙያ "የንስር አይን" ብዬ እይታውን እያደነኩ አካዳሚም ከገባ በኋላ አካዳሚውና ለልጁ እዚህ ደረጃ መድረስ አስተዋፅኦ ያደረጉ ከውስጥም ከውጭም ያሉ በሙሉ ሊመሰገኑ ይገባል እላለሁ።

መልካም የውድድር ዘመን!!

@ethio runners


https://www.facebook.com/100068870753847/posts/pfbid02ADEW8sA4JKE38VdcW8NmgD9ZJZ1GdLNvm9SbD1kRkGMSJxugw9n2h68yBpzP6s38l/?app=fbl
201 views21:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 10:02:31 ሐምሌ 02/2014 ዓ.ም

የ1443ኛው የኢድ አል አደሃ (አረፋ )በዓል በጉመር ወረዳ በተለያዩ አካባቢዎች በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት ከሚከበሩ አበይት በዓላት አንዱ የአረፋ በዓል ሲሆን 1443ኛው የኢድ አል አደሐ አረፋ በዓልን በጀመዓ ሶላት በወረዳው በተለያዩ አካባቢዎች በድምቀት ተካሂዷል።

የሰላት ፕሮግራሙ በሰላም ተጠናቆ ህዝበ ሙስሊሙ ወደ ቤቱ ተመልሷል።

በድጋሚ ኢድ ሙባረክ


https://www.facebook.com/100068870753847/posts/pfbid0MMsBT9HPFVXhzxmXr1BNCqkSvS9JGDaExmNu6ruGqoGgmwim6VXTbv1ZVF6Rzxqul/?app=fbl
260 viewsedited  07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 18:38:54 ሐምሌ 1 /2014 ዓ.ም

ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል አድሀ በዓልን አቅመ ደካሞችን በመርዳት እንዲያሳልፍ የእስልምና ሀይማኖት አባቶች ጥሪ አቀረቡ

ህዝበ ሙስሊሙ የኢድ አል አድሀ /አረፋ/ በዓልን አቅመ ደካሞችን በማገዝና በመጠየቅ እንዲያሳልፍ የእስልምና ሀይማኖት አባቶች ሀጂ ሙፍቲ ዑመር ኢድሪስ እና ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ጥሪ አቀረቡ።

ሀጂ ሙፍቲ ዑመር ኢድሪስ እና ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 443ኛውን የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ምክንያት በማድረግ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ህዝበ ሙስሊሙ ነገ በመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በድምቀት የሚከበረውን ታላቁን የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም ወጥቶ አክብሮ በሰላም እንዲመለስ ጠይቀዋል፡፡

ሀጂ ሙፍቲ ዑመር ኢድሪስ እና ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ለኢዜአ በጋራ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት፥ ሰላም የሁሉም መሰረት በመሆኑ ሁሉም ለሰላም ዘብ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ታላቁ የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በፍቅር፣በአንድነትና በወንድማማችነት እንዲከበር ህዝበ ሙስሊሙ ኢትዮጵያዊ አንድነቱንና ወንድማማችነቱን መጠበቅ አለበት ብለዋል፡፡

ሀገር፣ ቤተሰብ፣ልማትና እድገት የሚኖረው ሰላም ሲኖር በመሆኑ ለሰላም ከፍ ያለ ዋጋ በመስጠት በሰዎች መካከል የትብብርና ወንድማማችነት መንፈስ ማስፈን ይገባልም ነው ያሉት።

ህዝበ ሙስሊሙ ታላቁን የአረፋ በዓል ሲያከብር አቅመ ደካሞችን በመጠየቅ፣ የተራቡትን በማብላት፣ የታረዙትን በማልበስ መሆን እንዳለበትም አስገንዝበዋል።

ሀይማኖት የሚኖረው ሀገር ሲኖር መሆኑን በመረዳት በዓሉን ስናከብር በመተዛዘን፣ በመረዳዳትና አንድነትን በማጠናከር መሆን አለበትም ነው ያሉት በመልዕክታቸው።

የሀይማኖት አባቶቹ 1 ሺህ 443ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል የሰላም፣ የደስታ፣ የብልጽግናና የመከባበር ይሆን ዘንድ የትብብር መንፈስ መጎልበት አለበት ብለዋል፡፡(ኤፍ ቢ ሲ)

- ኢትዮጵያን እናልማ!
- የፈረሰውን እንገንባ!
- ለፈተና እንዘጋጅ!!

በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100068870753847
Telegram:- https://t.me/gummerw
Youtub: -https://youtube.com/channel/UCyqat__kk7lXxzpRv8r7chA
253 views15:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 17:33:29 ሐምሌ 1/2014 ዓ.ም

የጉመር ወረዳ መንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች መልካም የኢድ አል አደሀ አረፋ በአል ይመኛል።
በድጋሚ ኢድ ሙባረክ

- ኢትዮጵያን እናልማ!
- የፈረሰውን እንገንባ!
- ለፈተና እንዘጋጅ!!

በተጨማሪም እነዚህ ሊንኮችን በመጫን ወቅታዊና ትኩስ መረጃዎቻችንን እንድትከታተሉ እንጋብዛለን፡፡
Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=100068870753847
Telegram:- https://t.me/gummerw
Youtub: -https://youtube.com/channel/UCyqat__kk7lXxzpRv8r7chA
187 views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ