Get Mystery Box with random crypto!

ተዋህዶ PICTURES

የቴሌግራም ቻናል አርማ gs19religion — ተዋህዶ PICTURES
የቴሌግራም ቻናል አርማ gs19religion — ተዋህዶ PICTURES
የሰርጥ አድራሻ: @gs19religion
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.05K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ምን ይቀርባል?
1. የየእለቱ አመታዊ እና ወርሀዊ የቅዱሳን በዓለት
2. መንፈሳዊ ፎቶዎች [ በኛ በራሳችን የተዘጋጁ ]
3. መንፈሳዊ ፅሁፎች [ ሰኞ፣ እሮብ እና አርብ ]
4. ✞ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ መዝሙሮች እና ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት ቻናላችንን ይጎብኙ፡፡
እስትንፋስ ያለው ሁሉ እግዚአብሔርን ያመስግን" መዝ 150÷6

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 16:40:52 https://vm.tiktok.com/ZMNc3qFSJ/
151 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , 13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 20:33:27 ​​እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

#ልደት

መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል።

በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል።

ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል።

#ዕድገት

የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል።

#መጠራት

አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ።

የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ።

#አገልግሎት

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት።

1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል።

2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር።

ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል::

#ገዳማዊ ሕይወት

ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል።

እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል።

በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል።

#ስድስት_ክንፍ

ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር::

የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር።

ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:-
-በቤተ መቅደስ ብስራቱን
-በቤተ ልሔም ልደቱን
-በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን
-በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን
-በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር።

የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው።

#በዚያም :-
-የብርሃን ዐይን ተቀብለው
-6 ክንፍ አብቅለው
-የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው
-ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው
-ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው
-ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው
-"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል።

#ተአምራት

የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው።
ሙት አንስተዋል
ድውያንን ፈውሰዋል
አጋንንትን አሳደዋል
እሳትን ጨብጠዋል
በክንፍ በረዋል
ደመናን ዙፋን አድርገዋል።

ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና::

#ዕረፍት

ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል።

ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል።
226 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , edited  17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 20:33:26 የነሐሴ ተክለሃይማኖት ወረብ

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
@gs19religion
177 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , edited  17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 20:33:26 ነሐሴ ተክለሃይማኖት ምልጣን

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
@gs19religion
174 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , edited  17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 20:33:26 +++ የነሐሴ 24 አቡነ ተክለ ሃይማኖት ማኅሌት +++

መልክዐ ሥላሴ

ሰላም ዕብል ለንዋየ ውስጥ ምሕረትክሙ
ትሩፋተ ገድል ኩኑኒ ሥላሴ አምጣነ ትሩፋት አንትሙ፤
ሶበ ሖርኩሰ ከመ እሳተፍ ገድሎሙ፤
ጊዮርጊስ ኢወሀበኒ መጠነ ነጥበ ጠል እምደሙ፤
ወተክለ ሃይማት ከልአኒ ስባረ እምዐጽሙ፡፡
ዚቅ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤
ዘኢይነውም ትጉህ በውስተ ቅዱሳን ስቡሕ፤
ከመ ቀስተ ደመና የዓውዶ ሱራሄ ሎቱ ለባሕቲቱ ይደሉ ስባሔ፡፡

መልክአ ሚካኤል
1
ሰላም ለሕጽንከ እንተ በዲቤሁ ሕቁፍ፤
ጸሎተ ቅዱሳን ዉኩፍ፤
ሚካኤል ክቡር መስፍነ ትጉሃን አእላፍ፤
ለረዲኦትየ ከመ ዘይሰርር ዖፍ፤
እንዘ ትሰርር ነዓ በከልኤ አክናፍ፡፡
ዚቅ
ርድአኒ ወአድኅነኒ፤ ወሥመር ብየ፤
በከመ ሠመርኮሙ ለቅዱሳን አበውየ፡፡
2
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ . . .
ዚቅ
አመ ኖኅ ይእቲ መድኀኒት፤
እንተ ኮነት አንቀጸ ሕይወት ማርያም ቅድስት፡፡

መልክአ ተክለ ሃይማኖት
3
ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘጥንተ ፊደሉ መስቀል፤
ስም ክቡር ወስም ልዑል፤
ተክለ ሃይማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል፤
ከመ እወድስከ መጠነ አውሥኦተ እክል፤
ማእሠረ ልሳንየ ትፍታሕ ማርያም ድንግል፡፡
ዚቅ
ወንጌለ መለኮት ሰበከ ስምዐ ጽድቅ ኮነ
ወበእንተዝ ተክለ ሃይማኖት ተሰመይከ
4
ሰላም ለአዕይንቲከ ዘአርአያሆን ሐዋዝ ፤
እለ ጽዱላት እማንቱ ከመ ሰርቀ ቤዝ፤
ተክለ ሃይማኖት ኅብዓኒ እሞተ ኃጢአት አዚዝ፤
ለከሰ አኮ ከመዝ፤
ኢይረክበከ ሞት ዳግመ እምዝ፡፡
ዚቅ
ዳግመ እምዝ ኢይረክቦ ሞት ከመዝ ዳግመ እምዝ፡፡
5
ሰላም ለኵልያቲከ ዘፈተኖን በትዕግሥት፤
ኢየሱስ ክርስቶስ አበ ብርሃናት፤
ተክለ ሃይማኖት ሰጋዲ ከመ መላእክት፤
ጸሎትከ ዘገበርካሃ እስከነ ኍልቈ ምእት ዓመት፤
መድኀኒተ ትኩነነ እምግሩም ቅሥት፡፡

ዚቅ
ተክለ ሃይማኖት ሰማዕት ሰባኬ መድኀኒት
ጸሎትከ ትኩነነ ፀወነ እመንሱት
ተክለ ሃይማኖት ሰባኬ መድኀኒት
6
ሰላም ለጸአተ ነፍስ በስብሐተ አእላፍ እንግልጋ፤
ለዓለም ዛቲ እምግብርናቲሃ ወፁጋ፤
ተክለ ሃይማኖት ቶማስ ለመርዓስ ዐቃቤ ሕጋ፤
ለእለ ገብሩ ተዝካረከ እንዘ ሀለው በሥጋ፤
ሀቦሙ እግዚእየ ሞገሰ ወጸጋ፡፡
ዚቅ
ወወጽአት መንፈሱ ሶቤሃ፤
ወተቀበልዎ መላእክት በስብሐት ወበማኅሌት፤
እንዘ ይብሉ ሃሌ ሉያ፤
ወአብእዎ ኢየሩሳሌም ሰማያዊተ፡፡
7
ሰላም ለበድነ ሥጋከ ኤልሳዕ መምህር ዘገነዛ፤
በሠናይ ጼና መዓዛ፤
ተክለ ሃይማኖት ሰባኪ ፊሊጶስ ዘብሔረ ጋዛ፤
ለሥጋየ መሬታዊት አመ የኃልቅ ዕዘዛ፤
ስብረተ ዐጽምከ ይኩነኒ ቤዛ፡፡
ዚቅ
ሖረ ኀቤሁ ለተክለ ሃይማኖት ቀዲሙ ሌሊተ፤
ኤልሳዕ ስሙ መልአኮሙ ለአርድዕት፤
ውእቱኒ አምጽአ ከርቤ አፈዋተ፤
ገነዝዎ በሰንዱናት ለተክለ ሃይማኖት፡፡
7
ሰላም ለግንዘተ ሥጋከ በዘቦቱ ይትመሐፀኑ፤
ነገሥተ እስራኤል ኄራን ዘአስተሣነይዎ በበ ዘመኑ፤
ተክለ ሃይማኖት ሠዋዒ ለእግዚአብሔር ካህኑ፤
አድኅነኒ እምፀብአ ከይሲ ዘዐሥር ቀርኑ፤
ወእምብእሲ ዘክልኤ ልሳኑ፡፡
ዚቅ
መላእክት አእመሩ ሃይማኖተከ፤
ነገሥት ሐነፁ መካነከ፤
አባ ተክለ ሃይማኖት ክርስቶስ ዘአፍቀረከ፡፡
8
ሰላም ለመቃብሪከ እምቅድመ ትኑም ውስቴታ፤
ታቦተ ማርያም ድንግል ዘአንበርከ በውሳጢታ፤
ተክለ ሃይማኖት አቡየ ለወልድከ ዕጓለ ማውታ፤
ለበረከትከ ይከልለኒ ረድኤታ፤
ወይዑደኒ ዘጽድቅከ ወልታ፡፡

ዚቅ
ጸለየ ተክለ ሃይማኖት እንዘ ይብል ኀበ ተቀብረ ሥጋየ
ወተክዕወ ደምየ ህየ ይኩን በረከት፡፡
9
ሶበ አዕረፈ ተክለ ሃይማኖት ከዊኖ ህልወ በጾማዕቱ፤
እንዘ ርኁብ ወእንዘ ጽሙዕ ውእቱ፤
ላእካነ ማርያም አሜሃ እለ መጽኡ ለአፍልሶቱ፤
ተበሀሉ በአርጋኖን ወዘመሩ ሎቱ፤
አማን ለጻድቅ ክቡር ሞቱ፡፡
ዚቅ
ይቤሎ ኢየሱስ ለተክለ ሃይማኖት፤
ሰማዕኩ ጸሎተከ ወስዕለተከ፤
እምብዙኅ ፃማ አአርፈከ፤
ኀበ ሀሎ ፍሥሐ አነብረከ፡፡
+++
ምልጣን
አባ አቡነ፡ አቡነ መምህርነ እምአዕላፍ ኅሩይ፤
ሐውጽ እምሰማይ ብርሃነከ ከመ ንርአይ፡፡
ወይም
ሞቶሙሰ ለጻድቃን ሕይወቶሙ ውእቱ፤
እስመ ለጻድቅ ይትሌዓል ቀርኑ በክብር
ጻድቃን እለ አሥመርዎ ለእግዚኦሙ ምድረ ብርህተ ወጽዕዱተ ይወርሱ፡፡
+++
እስመ ለዓለም
ደሪዖሙ ተዓጊሦሙ መጠዉ ነፍሶሙ ለሞት፤
እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ እም ፀሐይ ይበርህ ገጾሙ፤
እለ አጥረይዋ በትዕግሥት
ኦ እፎ አምሰጥዎ ለሞት ለመጽብብ ከመ ይባዕዎ ለመርህብ
ኦ እፎ አምሰጥዎ ለሞት ዓደዉ እሞት ውስተ ሕይወት
ኦ እፎ አምሰጥዎ እለ ጸውዖሙ ወይቤሎሙ ንዑ ለአቡየ ቡሩካኑ
እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ
አመ ያቀውም አባግዓ የማኑ ወአጣሌ በጸጋሙ
ኦ እፎ አምሰጥዎ ለሞት አሜሃ ይቤሎ እለ በየማኑ ንዑ ለአቡየ ቡሩካኑ
ወያወርሶሙ ምድረ ሐዳሰ እንተ ታውኅዝ ሐሊበ ወመዓረ
ኦ እፎ አምሰጥዎ ለሞት ገነተ ትፍሥሕት ኪያሃ አውረሶሙ ወአቀቦሙ ከመ ብንተ ዐይን ለጻድቃን እለ ሎቱ ተቀንዩ በሕይወቶሙ፡፡
+++

ለወዳጅዎ ሼር ያድርጉ!
@gs19religion
204 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , edited  17:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 18:27:17 በምን ልመስልሽ

ክፍል ፩
217 viewsNÃTAÑAM, edited  15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 14:04:24 https://vm.tiktok.com/ZMNWYcMQg/
303 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , 11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 14:04:14 https://vm.tiktok.com/ZMNWYcMQg/
298 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , 11:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 14:02:27 https://vm.tiktok.com/ZMNW28H95/
301 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , 11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 08:48:09 እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል አደረሳችሁ!!!

#ድንግል_ሆይ የአንቺ ሥጋ ይገርመኛል ከሔዋን ተገኝቶ ከመላእክት ይልቅ ንፁህ ሆኗአልና፣ አፈር ነህ ከተባለው ከአዳም ተወልደሽ በሰማይ በአባቱ ቀኝ በተቀመጠው ንጉሥ በክርስቶስ ክቡር ሰውነት ላይ በተለየ ክብር ሆኖ በሰማያት ታይቷልና። ባለ ራዕይው ዮሐንስ ከአንቺ በነሳው ሥጋ ከተወጋው ቁስለቱ ጋር ወደ ሰማይ እንደወጣ ቢያየው እንዲሁ ይመጣል ብሎ በመፅሐፍ ነገረን። የወጉትም ሁሉ ያዩታል ተብሎ ተፃፈ። የታናሿ የአንቺ ገላ ሰማይ ለሚጠበው አምላክ ልብስ ሆነ። መሰወሪያው ከዚህ ነው የማይባለው ልዑል ሥጋሽን ለብሷልና ሥጋ ሆነ ተባለለት። ከባሕሪው እሳት የሆነውን እርሱን ሁሉ ዳሰሰው ሁሉ አቀፈው። መለኮታዊ ክብሩን በአንቺ ሥጋ ውስጥ ቢሰውረው የወደቀው ሰውም አምላክ ሆነ ተባለ። ይደንቃል።

#ደንግል_ሆይ መላእክት በቤተልሔም በአንቺ ላይ የሆነውን ቢመለከቱ ስብሐት ለእግዚአብሔር አሉ። ሌላ ምን ይባላል? የማይወርደው ከከፍታው ወርዶ ሲታይ በአድናቆት ስብሐት ነው እንጂ። ሰማይ ከክብሩ የተነሳ የምትጠበውን በአንቺ ክንድ ላይ ሲያዩት ምን ይበሉ? ኦ ማርያም በአንቺ የሆነውን ለመፃፍ የሚያስብ ቃለ ፀሐፊ ከፍቅሩ የተነሳ ብዕሩ በእንባ ስለሚርስ ስለ አንቺ እንዲህ ነው ለማለት ቃልና እቅም በማጣት ሰአሊ ለነ ብሎ ጽሑፉን ይዘጋዋል። አይችልምና።
@zemariian
#ልዑሉን_የወለድሽ_ልዕልት_ሆይ የአንቺ ሥጋ ከአቤል ይልቅ ተወደደ፤ ከደገኛው አብርሐም ይልቅ ከፍ አለ፤ ከንጉሱ ከዳዊት ይልቅ ሥጋሽ የተለየና የተመረጠ ሆነ ...ዳዊትም፦ ንጉስ ደም ግባትሽን ወደደ ብሎ ፃፈልሽ። ከእስራኤላውያን አባት ከያዕቆብ ድንኳን ይልቅ የአንቺ ሥጋ ተመረጠ። ሎጥ፦ መላእክትን ወደ ቤቴ ግቡ ቢላቸው በአደባባይህ እንሆናለን እንጂ አንገባም አሉት። ድንግል ሆይ የአንቺ ሥጋ ግን መላእክትን ለፈጠረ ጌታ ማደሪያ ሆነ። ለዚህ ቃል የለም ዝምታና አንክሮ እንጂ።

#ድንግል_ሆይ የአንቺን ሥጋ በመቃብር የለም በአብ ቀኝ እንጂ። አንዳንዶች ተነስታለች ለማለት ከበዳቸው። ለመሆኑ ልጅሽ አልዓዛርን ከመቃብር ያስነሳ መሆኑን አላነበቡ ይሆንን? የኢያዒሮስ ልጅን ታሪክ አልተመለከቱ ይሆን አንቺ ግን ወደ ሰማያት ከተነጠቁት ከሄኖክና ከኤልያስ ትበልጫለሽ።
የቅዱሳን ሐዋርያት አባቶቻችን በረከት የእመቤታችን ረድኤት አይለየን አሜን!!!

#ድንግል ሆይ ምልጃሽ #ኢትዮጵያን #ይታደግ። ለዓለም ምሕረት ይሁን ።
313 views𝖌𝖊𝖟𝖚 , edited  05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ