የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
1.73K
የሰርጥ መግለጫ
ይህ የአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ጉባዔ መንፈሳዊ ትምህርቶች እና መልዕክቶች እንዲሁም ወቅታዊ መረጃዎችን የሚያስተላልፍበት ይፋዊ(Official) የቴሌግራም ገጽ ነው።
ማንኛውንም አስተያየት ፥ ሀሳብ እና ጥያቄ ካለዎት @AstugibigubaeBot ላይ ያድርሱን::
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
1
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-07-01 08:24:21
የአዳማ/ሳ/ቴ/ዩኒቨርስቲ ግ/ጉባኤ pinned a photo
05:24
2022-07-01 08:24:08
ውድ ተማሪዎች እንኳን ለጻድቁ አባታችን ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት በሰላም አደረሳችሁ ።
ዛሬ በ24 -10-2014 ዓ.ም ግቢ ጉባኤያችን የ5ኛ ዓመት ልጆቿን ለክብር ስለበቁ ደስታዋን ታያለች ። እነሆ ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ ( መዝ ፻፲፯÷፳፮ ) እያለች አበባዋን ልታይ ሰዓታትን ብቻ እየጠበቀች ነው ።
በመሆኑም ውድ በግቢ ያላችሁ ከ 1ኛ እስከ 4ኛ ዓመት ድረስ ያላችሁ ተማሪዎች ዛሬ ምሽት 10:30 ጀምሮ በገዳ በር ተገናኝተን በዝማሬ እና በእልልታ ወደ እናታችን ቤት ሙሽሮቿን አጅበን ስለምንሄድ ሁላችንም እንዳንቀር አደራችን የጠበቀ ነው ።
የታላላቆቻችንን ደስታ ደስታችን ነው እና በሰዓት በመገኘት የደስታቸው ተካፋይ እንድንሆን ስንል ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ።
ውድ ተመራቂዎች እንኳን ደስ ያላችሁ
489 viewsማኔ ቴቄል ፋሬስ, 05:24
2022-07-01 08:19:12
የአዳማ/ሳ/ቴ/ዩኒቨርስቲ ግ/ጉባኤ pinned Deleted message
05:19
2022-06-30 22:22:32
ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ
ዓርብ በ24/ 2014 ዓ/ም በተክለሃይማኖት ቤ/ት ልዩ የምረቃ ሥነ ስርዓት ይካሔዳል።
የ2014 ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ!!! እንቋዕ ተፈሳይክሙ!!!
እነሆ ነገ ዓርብ በአዲሱ የዩኒቨርሲታችን በር (ገዳ በር) 10፡30 ላይ ተገናኝተን እየዘመርን ወደ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ እንሔዳለን። በአባቶቻችንም ተባርከን ፤ ተቀድሰን፤ "በእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ" ተብለን ተመርቀን እመለሳለን። በመሆኑም ሁላችንም እየተቀሳቀስን በእግዚአብሔር ቤት ተመርቀን እንመጣ ዘንድ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን!
ልብ ይበሉ 10፡30 ላይ ጉዞ የምንጀምርበት ነው!
792 viewsTensay Ayalew, 19:22
2022-06-23 23:13:29
ህይወት ከምረቃ በኋላ ምን ዓይነት ገጽታ ሊኖረው እንደሚችል አስበውት ያውቃሉ? የእርስዎስ ህይወት ከምረቃ በኋላ ፍልስፍናዎ ምንድን ነው? ከግቢ ከወጡ በኋላ ስለሚኖርዎት ሕይወት አቅጣጫ አስቀምጠዋል? ለማንኛውም ቅዳሜ ምሽት 11፡30 በተክለሃይማኖት ቤ/ክ ተመርቀው በሕይወት እየኖሩበት ባሉ ታላላቅ መምህራን በጋራ ስለምናየው እንዳይቀሩ። ታዲያ ሲመጡ ጓደኛዎትን ይዘው መምጣቱን በእግዚአብሔር አደራ እንላለን።
806 viewsTensay Ayalew, 20:13
2022-06-23 10:48:08
ኪዳነ ምሕረት
እመብርሃን
ወላዲተ አምላክ ሆይ
በተሰደደ ጊዜ ለአዳም ተስፋው
ለበላኤ ሰብ ጭንቅ አማላጅ
ለአባ ኅራያቆስ ለኤፍሬም ለቅ/ያሬድ የእውቀት ብርሃን በር ከፋች
ለተማሪ እራቱ የሆንሽ እኔንም ኃጢያተኛ ልጅሽን
ልጅሽ ወዳጅሽ ጸጋውን እና ምህረቱን ያበዛልኝ ዘንድ
እንደ ባቢሎን ግንብ ከተቆለለው የጢያቴ ክምር አውጥቶ ወደ ቀናው መንገድ ይመራኝ ዘንድ የቀናውንም መንፈስ በውስጤ ያድስ ዘንድ
ቅድስት ሆይ ለምኝልኝ!!!
የቅድስት ኪዳነ ምሕረት የእመ ብርሐን ልጆች
ሐሙስ በ16/10/2014 የኪዳነ ምሕረት ጽዋ
12፡00
አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ
የእመ ብርሐን ጸሎቷ በረከቷ አማላጅነቷ አይለየን አሜን!!!
770 viewsTensay Ayalew, 07:48
2022-06-23 09:30:40
ለምርቃት የሚቀርብ ወረብ
599 viewszeddd A, 06:30
2022-06-23 09:29:31
ሐዋርያተ ሰላም ብርሃናተ ዓለም ብርሃናተ ዓለም/2/
አስራበ ምሕረት ከአው ከአው እምአርያም/2/
542 viewszeddd A, 06:29
2022-06-21 09:06:40
721 viewsTensay Ayalew, 06:06