2023-07-06 10:25:10
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች
የኢኮኖሚ ዘርፍ ዋና ግብ በአድርጎ የተነሳነው የግሉን ዘርፍ ማነቃቃት ነው፣
ማክሮ ኢኮኖሚ ላይ የተፈጠሩ ስብራቶችን ማሻሻልና ምርታማነትን ማብዛት፣
ሁለተኛው ሀገር በቀል ማሻሻያ እቅድ ዋና ግቡ የኢኮኖሚ ስብራቶችን መጠገን ነው፣
የመጀመሪያው አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ ይዞት የተነሳው አላማ የግሉን ዘርፍ ማነቃቃት ዋና ግቡ ነበር፤ ሁለተኛው ግቡ የተሰበሩ ኢኮኖሚዎችን ማነቃቃትና መጠገን፤ ሶስተኛው በሰፊውና በብዝሃ ዘርፍ ምርታማነትን ማሳደግ ነው፣
ይህ እቅድ በርካታ ሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ተግዳሮቶች ቢገጥሙትም በምክክር ቤቱ አባላት እንደተነሳው ብዙ ጥቅሞች አስገኝቷል፣
ሁለተኛው አገር በቀል ማሻሻያ ዋና ግቦቹ የኢኮኖሚ ስብራቶችን መጠገን ነው፡፡
የዘንድሮ በጀት የቀረበው የሶስቱን አመት ማሻሻያ የአለምን እድገትን በሚመለከት ብዙ ትንበያ ተሰጥቷል፣
በአለም እድገት እያመጡ ከተባሉ ሀገራት መካከል አንዷ ኢትዮጵያ ናት፣ በዚህ አመት 7 ነጥበ 5 እድገት ይመጣል ብለን እንጠብቃለን፣
ግብርና በኢትዮጵያ ውስጥ 33 በመቶ ድርሻ፤ ኢንዱስትሪ 28 በመቶ፣
ግብርና 6.3 በመቶ እድገት ያመጣል፤ በሩዝ በስንዴ በማር በዶሮ እርባታ ከፍተኛ ለውጥ ታይቷል
በኢንዱስትሪ ዘርፍ 160 ፋብሪካዎች ስራ እንዲጀምሩ ተደርጓል፣
የዋጋ ንረት በየትኛውም ሀገር ችግር ነው፤የዋጋ ንረት ያልነካው ሀገር የለም፣
የውጪ ምንዛሩ እጥት ያጋጠማቸው 90 ሀገራት ለክፉ ቀን ብለው ያስቀመጡትን አውጥተው ተጠቅመዋል፣
እነዚህ 90 ሀገራት 80 በመቶ የእነሱ ሀገር ከረንሲ ቀንሷል፣ ለዚህም ነው በዶላር መገባያየት ማቆም አለብን የሚለው የሚሰማው፣
ከ90 ሀገራት መካካል 60 ዎቹ እዳ አለባቸው ከእነሱም ውስጥ 20 ዎቹ እዳ መክፈል አልቻሉም፣ በዚህ ውስጥ የኢትዮጵያን ነገር ማየት ያስፈልጋል፣
1.3K viewsEnoch חנוך Ενώχ, 07:25