Get Mystery Box with random crypto!

ጥብቅ ሚስጥር ነው! ዳንኤል ብርሃነ ወደ ምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል ነው ያደገው። ሌሎች የትህነግ | Getachew shiferaw

ጥብቅ ሚስጥር ነው!

ዳንኤል ብርሃነ ወደ ምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል ነው ያደገው። ሌሎች የትህነግ ሰዎች ለመግለፅ የማይደፍሩትን ሚስጥር ዘረገፈው! የሰምኑ ወረራም የሌላው ችግር ምንጭ ይህ ዳንኤል የነገረን አካሄድ ነው!

1) ትህነግ ስምምነቱ በተለይም ትጥቅ ማስፈታቱን ጨምሮ ሌሎችን በጓዳ ውል እንዲዘገይ ያደረገው በእርዳታና ብድር መሆኑን በራሱ ተሞክሮ ይነግረናል። ዳንኤል የአውሮፓውን ዲፕሎማት በብድርና እርዳታ ጫና አድርገልን ያለው በራሱ ተነሳሽነት አይደለም። የዋናው ትህነግ መጫዎቻ ስለሆነ ነው። የኦሮሞ ብልፅግና ካለው ፀረ አማራ ፍላጎት ባሻገር፣ ትህነግ ትጥቅ መፍታቱንም ሌላውንም በጓዳ ውል ያስቆየው በዚህ መንገድ ነው። ዲፕሎማቶች በየቀኑ ወደ መቀሌ ሲመላለሱ ለዚህ እንደሆነ ብልፅግና ያውቃል። ፍላጎቱም ነው።

2) ዲፕሎማቶቹም ሌላ ጥያቄ ሲጠየቁ ያለምንም ማወላዳት "ትጥቅ አትፈቱም" የሚሉት የትህነግ የመጀመሪያ ፍላጎት እንደሆነ ስለሚያውቁ ነው። ብልፅግናም በጓዳ የተዋዋለው፣ የአማራን ርስቶች ለብድርና እርዳታ ቀብድ ያደረጋቸው መሆኑን ማሳያ ነው።

3) ሰሞኑን ጨምሮ በተለያዩ ጊዜያት የአማራን ርስቶች አሳልፎ የመስጠት የአብይ አህመድ እና የትህነግ የጓዳ ውል ተግባራዊ እንዲሆን የሚደረገው አብይ ብድርና እርዳታ ሲፈልግ፤ የሞቀ ድርድር ላይ ሲሆን ነው። የሰሞኑ የራያና የሌሎች አካባቢዎች ወረራ አብይ ከዓለም የገንዘብ አበዳሪዎች ጋር ሲደራደር የተፈፀመ ነው። ዳንኤል ያወጣው ሚስጥርም ከዚሁ ጋር የተገናኘ ነው።

4) እየተተገበረ ያለው የሰላም ስምምነት አይደለም። አብይ የአማራን ርስቶች በብድርና እርዳታ፤ በጓዳ ውል ከሰላም ስምምነቱ በተቃራኒ አሳልፎ ነው እየሰጠ ያለው።

ዳንኤል በግልፅ ተናገረው እንጅ የምናውቀው ነው። ዳንኤል ያወጣው ዲፕሎማቶቹ በትህነግ የሚነገራቸውንና እየሆነ ያለውን እውነታ ነው። ይህ ቀላል ጉዳይ አይደለም። ጥብቅ ሚስጥር ነው!