የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም መጠናቀቁን ፖሊስ አስታወቀ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይና በተለያዩ ቦታዎች የተከበረው የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ መስከረም 16 ቀን 2015 ዓ.ም የሃይማኖት አባቶች፣ የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮችና በርካታ የእምነቱ ተከታዮች በተገኙበት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይና በተለያዩ ቦታዎች የተከበረው የደመራ በዓል በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡ የፀጥታ አካሉ ዕቅድ በማውጣት በርካታ የሰው ኃይሉን በመከላከል ስራ ላይ ማሰማራቱን፤ ከበዓሉ አስተባባሪዎች ጋር በቅርበት በጋራ በመሰራቱ በአዲስ አበባ የተካሄደው የደመራ በዓል ፍፁም ሰላማዊ ሆኖ መከበሩን ፖሊስ ገልጿል፡፡ @gasha_tube 421 views𝖊𝖙𝖍𝖎𝖔 𝖆𝖑𝖎𝖇𝖆𝖇𝖆 Тєαм, 06:08