Get Mystery Box with random crypto!

ፍቅር እና ጠበሳ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fonkabcha1 — ፍቅር እና ጠበሳ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fonkabcha1 — ፍቅር እና ጠበሳ
የሰርጥ አድራሻ: @fonkabcha1
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.10K
የሰርጥ መግለጫ

😘ወንዱ ሴት ለማናገር ብለህ ወሬ ጠፍቶብህ ትደናበር ይሆን ሴቱአስ እንደወንዱ ሆነሽ ታቂያለሽ?
😘 ሴት ልጅ ወደ አንተ መሳብ እንዴት እንደሆነ ያቅትህ ይሆን አንቺስ ያቅትሽ ይሆን?
😘 ፍቅር ማለት ምን ማለት እንደሆነ አታቁም ይሆን?
አያሳስባቹ ቤተሰባዊ ቻናል ይቀላቀሉን።
😘ለማንኛውም መልእክት ሆነ አስተያየት 👇👇👇👇👇
@Amirlovelys

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-23 20:20:32 ​​​​​​​​​​​​​​​​


ሴትን አላምንም

ክፍል  18

ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ

እነሆ የማጣሪያው ወቅት ደርሶ የሀኪሙ ጉሮሮ ድምፅ አሰማ ፤ ያ ተስፋችንን የያዘው ወረቀት አለው የሚመስል ድምፁን አስተጋባ ፣ የክፍሉ ግድግዳዎች የእኛን ውጤት ለመስማት አሰፍሰፈው እየጠበቁ ይመስላሉ ፤ እንኳን ደስ አላችሁ ሊሉን አልያም አላህ ያበርታችሁ ሁሉንም የሚያደርገው አላህ ነው በርቱ ሊሉን የተዘጋጁ ይመስላሉ ፤ ውጪ የቆመው ሰው የእኛን ውጤት ለመስማት የተሰበሰበ መስሎ ታየኝ ፤ የእናቴ ድምፅ ጆሮዬ ጋር እያስተጋባ ይሰማኛል ፤ "አላህ ያሻውን ሰሪ" ነው በአላህ ውሳኔ ፅኑ ብላ መክራኝ ድምፇ የተሰወረ መሰለኝ።

አህላምዬ ጨንቋታል አይኗ አንዴ ሀኪሙን አንዴ እኔን ቀጥላ ደግሞ አይኗን ሰበር አድርጋ ወረቁቱን እያየች እጆቿን አቆላልፋ በረዥሙ ትተነፍሳለች ፤ እኔም ፍርሃቴ እሷን ባየው ቁጥር እየጨመረ መጣ ፤ ችግሩ ከእኔ ከሆነ ሌላ የህይወት ፈተና ሊጋረጥብኝ እንደሆነ እየተሰማኝ ነው።

 ያ በፍቅር ብርሃን ደምቆ የቆየው ቤታችን ጨለማውን ጥሎ ለዚህ የበቃው የትዳር ጐጆአችን ሲንገጫገጭ ተሰማኝ ፤ ችግሩ በእርሷ በኩል ከሆነ ከአጠገቧ ላልለይ ቃል ገብቻለው ፤ አዎ ዓላማችን በፍቅር የተሞላ ትዳርና በትዳር ውስጥ ልጅ መመስረት እንጂ በልጅ መምጣት እና ባለመምጣት ውስጥ የሚበተን ቤተሰብ አልነበረም ፤ ቢሆንም የእኔ "አህላም" ሴት ናት ታድያ መውለድ አትችይም ቢላት ተስፋ አትቆርጥም? አታዝንም? የህይወት ውሉ አይጠፋትም? ግን እኔስ የትኛውስ የልጅ ፍላጐትና አምሮት ቢኖረኝ አህላምዬን ገፍቼ የምሄድ ዓይነት ሰው ነኝ?እላለው።

 ብቻ እርሷ ደህና ትሁንልኝ እልና መለስ ብዬ ደግሞ "ችግሩ በእኔ ምክንያት ከሆነ ከጊዜያት ቡኃላ ፀባያቸው የተቀያየረው ቤተሰቦቿ ሌላ ምክንያት አግኝተው አህላምዬን ሊነጥቁኝ ሊያሰፈስፉ ይችላሉ  ብዬ ስጋት ይዞኛል ፤ ስራዬ ከተባላሸ ቡኃላ የቤተሰቦቿ ጣልቃ ገብነት ከመቼውም ጊዜ በላይ ኃይሏል ፤ ሀኪም ቤት ውስጥ በድን አካሌ አለ እንጂ ልቤ ብዙ ቦታዎች ደርሶ መመለሱን ተያይዞታል  ።

ዶክተሩ ረጋ ባለ ድምፅ ውጤታቹ ደርሶኛል አብረን እንየው ምን ትላላችሁ ? አለ

ድንገት ቀዝቃዛ ውሀ እንደፈሰሰበት ሰው ብንን ብዬ ከሃሳቤ መለስ አልኩኝ ፤ ለምን ረጋ ባለ ድምፅ ይናገራል? ለምንስ ጮክ ብሎ ውጤታችን አይነግረንም? ውጤታችን መጥፎ ስለሆነ ነው ሀዘን በቀላቀለበት ድምፅ " ውጤታቹ ደርሶኛል አብረን እንየው" ያለው? ብቻ ዶክተሩ እጅ ላይ ያለው የታሸገ ወረቀት እንጂ ሌላ አይደለም ፤ እርሱም ስላላየው ይሆናል ውጤታችንን አብረን እንየው ያለው። 

አህላምዬ እጄን ይዛ ውጤቱን ለመስማት አይኗን እና መላ አካሏን ወደ ዶክተሩ አዙራዋለች እጇ በጣም ይሞቃል ጣቶቿም መንቀጥቀጥ ጀምረዋል ።

ዶክተሩ የእኛን ምላሽ ሳይጠብቅ ንግግሩን ቀጠለ
" ውጤቱ ምንም ይሁን የእናንተ ትዳር የተመሰረተው ለፍቅር እንጂ ለልጅ አይደለም ፤ ልጅ መሰረታዊ ነገር ቢሆንም ግን ፍቅር ከሁሉ ይልቃል ፤ በህይወት ውስጥ ጥሩም መጥፎም  አጋጣሚዎች ይከሰታሉ ፤ እዚህ ወረቀት ውስጥ ያለው ነገር መጥፎም ጥሩም የሚያደርገው ጭንቅላታችሁ ነው። ይህ ውጤት መውለድ አትችሉም የሚል ቢሆን ወይም አንተ ላይ አልያም እርሷ ላይ ነው ችግሩ ያለው ቢል የሆነው ሁሉ እናንተ ፈልጋችሁ ያደርጋችሁት ሳይሆን ፈጣሪ ያደረገው ነው።  ሌላው ደግሞ በህክምና የማንደርሰበት ብዙ የራቁ ነገሮች ፈጣሪ ይኖረዋል ፤ መውለድ የምትችሉ ሆናችሁ ግን አዝግይቶ ሊያሳካው ይችላል። ስለ እውነት እዚህ ሀኪም ቤት ከ10 ዓመት በላይ ቆይተው መጥተው ምርመራ ያደረጉ ጥንዶችም አሉ የእናንተ ገና ወደ ሶስተኛ ዓመት መጠጋቱ እንደሆነ ነግራቹኛል ፤ ስለዚህ ውጤቱ መልካምም ሊሆን የሚችልበት አጋጣሚ ሰፊ ነው "መልካም ዕድል" ብሎ ወረቀቱን ቀደደው ፤ መብረቅ እንደወረደበት ሰው ፈዝዤ ቀረው ፤ ምን ሊል እንደሚችል መላምት ከመስጠት የእርሱን ምላሽ መስማት ፈልገኩኝ።

ዶክተሩ ረጋ ያለና ታማሚን በእርጋት የሚያዳምጥ ለታማሚዎች ከህክምና በላይ ስነ-ልቦናዊ ምክር መስጠት የሚቀናው ቀና ዶክተር ነው ፤ በዚህ ስራ ላይ የረዥም ጊዜ ልምድ ያለው ስለሆነ ሁሉም ሰዎች ይመርጡታል።

ዶክተሩ በረዥሙ ተንፍሶ ውጤቱን በወፍ በረር ቃኝው እና ንግግሩን ቀጠለ "የመኻንነት ችግር በጥንዶች ላይ ተከሰተ የምንለው በየጊዜው የወሊድ መከላከያ ሳይጠቀሙ ለአንድ ዓመት ግንኙነት ቢያደርጉም ጽንስ መፈጠር ካልቻለ ነው፡፡ ይህ ችግር የወንድም ሆነ የሴት ችግር  ሊሆን ይችላል፡፡ከዚህ ጋር ተያይዞ ዕድሜያቸው ከ35-40 ዓመት እና ከዚያ በላይ በሆኑ ጥንዶች ላይ ይህ ችግር የማጋጠም ዕድሉ የጨመረ ነው፡፡ 

ለመኻንነት ችግር መጋለጥ የዘረመል ችግር (genetic problem) ዋነኛ ምክንያት ሊሆን ይችላል፡፡

ይህ ደግሞ ምንም አጋላጭ ምክንያቶች ሳይኖሩ ሊፈጠር የሚችል ነው፡፡ ይህ ዓይነት መኻንነት (primary infertility) ወይም እርግዝና ተከስቶ የማያውቅበት ዓይነት የመኻንነት ዓይነቶች ውስጥ ዋነኛው ነው፡፡

ሌሎች የ"Primary infertility " ዓይነቶች
የዕንቁላል ማጠራቀሚያ ወይም የዕንቁላል ችግር ፣
የወንድ የዘርፍሬ አፈጣጠር መጠን እንዲሁም የዘርፈሳሽ አወራረድ ችግር ፣ በተለያዩ ምክንያቶች የማህፀን ቱቦ መደፈን ችግር እና በሰውነት እድገንጥ (hormone) መዛባት ምክንያት እርግዝና ያለመከሰት የመሳሰሉት ናቸው፡፡


አጠቃላይ የምርመራ ውጤታችሁ እንደሚያሳየው ዋነኛው የችግሩ ሰለባ ወይዘሮ አህላም መሆኗን ያመለክታል ፤ ይህ ያለመውለድ ችግር ደግሞ በእርሷ ላይ ተከስቷል አለን።


ልቤ ክው አለ አህላምዬን ቀና ብዬ ስመለከታት ዓይኗ ላይ ያቀረረው ዕንባ ገደቡን ጥሶ ፈሰሰ ፤ የፈራሁት አልቀረም መረጋጋት አልቻለችም።

 አህላምዬ እባክሽ ተረጋጊ እኔ ሁሌም ከጐንሽ ነኝ እያልኩኝ ለማፅናናት ሞከርኩኝ ፤ ግን እኔም ሀዘኗን መቋቋም አልቻልኩም ዕንባዬ ገንፍሎ ወጣ ማን ማንን ያረጋጋ።

እራሴን እንደምንም አረጋግቼ  መሀመድ ጋር ደወልኩለት ቶሎ እንዲመጣ ጠቁሜው ስልኬን ዘጋሁት። ማሜ  ሲከንፍ መጣ የሆነውን ሁሉ ስነግረው ውስጡ ተረበሸ ግን ቢያንስ እርሱ መረጋጋት እንዳለበት ስለገባው ሁለታችንንም ይዞን ወጣ ፤ አህላምዬ ዕንባዋ ያለ ገደብ ይፈሳል ጨንቀኝ ግን ምን ላድርግ ትንሽ ታልቅስ ይውጣለት አልኩኝ በልቤ።  ሆዷ ውስጥ እንዳይቀበር ፈልጌ ስለ ነበር ከወጣን ቡኃላ አልተጫንኳትም ፤  ያኔ  ከትምህርት ቤት አብረን በዛች ላዳ ስንመጣ እንዳደረገችው ትከሻዬ ላይ ተኝታ ታለቅሳለች ፤ ቤት ደርሰን ከመኪና ወርዳ በፍጥነት ወደ ውስጥ ገባች ፤ ማሜን የመኪና በር ከፍቼ ቤት ካስገባሁበት ቡኃላ ወደ ሳሎን ሮጬ ሄድኩኝ በር ላይ ስደርስ ከባድ ድምፅ ተሰማ......

ክፍል አስራ ስምንት ይቀጥላል ....... .......

@fonkabcha1
@fonkabcha1
227 viewsPassenger, 17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 15:39:08 ​​​​​​​​​​​​​​


ሴትን አላምንም

ክፍል 17

ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ


ያ እናቱን እና እህቱን በሞት የተነጠቀው ወጣት ነበር ፤ አዎ እርሱ ነው ግን እንዴት አዕምሮው ታወከ?  ምን ሆነ? እንዴት እንደዚህ?  ቤተሰቡን በማጣት ወይስ ሌላ አዲስ ነገር ? አላውቅም ብቻ ያ በተስፋ መቁረጥ ውስጥ የዕንባ ጎርፍ ፣ የሀዘን ደም ሲያነባ የነበረው ወጣት ያደፈ ልብስ ለብሶ ጭንቅላቱ ላይ ሰንደል አድርጎ ከሩቅ የማይታዩ ሁለት ፎቶዎችን ይዞ ፣ በጠቆረ እግሩ አስፓልቱን እየረገጠ "ሴትን አላምንም  ሴትን አላምንም " ይላል ፤ ምን ሆነ ለእዚህ ደረጃ ያደረሰው ቤተሰቡን መነጠቁ ነው ቤተሰብ እንደሌለው አውቃ ማንኛዋ ነች እንዳያምን አድርጋ የጎዳችው አልገባኝም "   ሀገር የሌለው ህዝብና ቤተሰብ የሌለው ሰው አንድ ነው። ቤተሰቦች የሰው ስብስብ እንደሆኑ ሁሉ ሀገርም የቤተሰቦች ስብስብ ናት። የቤተሰብ  ጥንካሬው የቤተሰቡ አባላት ሲሆኑ የሀገርም ጥንካሬ ቤተሰቦች መሆናቸው መርሳት የለበትም። ሰው ሲበላሽ ቤተሰብ ይበላሻል። ቤተሰብም ሲፈርስ ሀገር ይናዳል። ስለዚህ ሀገር እና ቤተሰብ ሲበላሹ ጥፋቱም ተመሳሳይ ነው የሀገር መበላሸት ሰበብ ቤተሰብ ሲበላሽ ነው።

በእርግጥ ሰው ያለ ሀገርም ያለ ቤተሰብም መኖር  ይችላል  ይህ ኑሮ ከተባለ ፤ ሀገርና ቤተሰብ ባይኖር ዓለም ምን ትመስል ይሆን?  ብቻ አላውቅም እርሱ ግን ቤተሰቡን ሀገሩ ነጠቀችው ፤ በሀገሩ ላይ በነፃነት መኖር ባይችልም በነፃነት ማበዱን ግን ብዙዎቹ አልነጠቁትም  ከህፃናቶቹ በስተቀር ፤ እርሱ ሲመጣ ህፃናቶቹ ከእርሱ ጋር እብደቱን ይጋሩታል ፤ ከመኖርያዬ አቅራብያ ላይ ነው እንዲ ሲሆን ያየሁት እንዴት እዚህ መጣ? እብድ መቼ አንድ ቦታ ይቆያል ፤ ያ ውብ ወጣት የያዛቸውን ፎቶዎች ዓየት እያደረገ ይጮሃል ያለቅሳል ፤ ፎቶዎን ለመጣል ወደ መሬት እጁን ይሰነዝርና መልሶ ፎቶዎችን እያየ አዎ "ሴትን አላምንም" እያለ ፎቶዎችን አቅፎ ያለቅሳል።

አይ ክፋት እነዛ ክፉዎች ህልሙን ነጠቁት ተስፋውን አጨልሙበት ፤ ህልሙን የተነጠቀ ተስፋው የጨለመ ስው ስለምንስ ያስብ ።

ሰው የዚህን ያህል ለምን ከፋ በሰው ስም መነገድ ብልጠት እራሳችንን ፣ ማስቀደም ብልህነት፣ በሌሎች ክብር ላይ ተረማምዶ ማለፈ  ክብር የሚያስገኝልን እየመሰለን ከሰብዓዊው ማንነታችን ቀስ በቀስ ሸሸን። ዕውነታው ግን ስለሰው መኖር ሌሎችን ማስቀደም ነበር ሰብዓዊነት።

ይህው ጥቅመኛ ባለስልጣኖች መንገዱ አበላሽተው እናቱን እና እህቱን ነጥቀው  ወጣትነቱን አባክነው እነርሱ ስጋ ይቆርጣሉ። ሁለት በሬ አንዱን ለለቅሶ ሌላኛው ለሰርግ ይታረዳል ፤ ይህ ወጣት ለእናቱ ሀዘን ለለቀስተኛው በሬ አረዶ ዛሬ ግን ራቆቱን ያወራል የእናት ሞት ያልገባቸው።  

በቅጡ አስታምሜ የቀበርኳት እናቴ ሞት እንኳን ያብከነክነኛል ፤ እንኳን በስህተት የሞተችበት እናቱ ያውም ያገለግሉናል ብለን በመረጥናቸው ሰው በሊታዎች።  ለማን ይነግሩታል የእናት ሞት ፤ እርሷ እኮ ከሌለች ቤት እኮ ባዶ ይሆናል ፣ ቀን እኮ ይጨልማል እናቴን አጥቼ ነው የምኳትነው ፤ ዱዓዋ ቀርቶብኝ ነው አይወጡበት ዕዳ ውስጥ የተዘፈቀኩት ፤ እናቴ ወላጅ ብቻ አነበረችም ሁለመናዬ ነበረች  ፤  ይህው ለሰው የማይነግሩት ሸክም ተሸክሜ በሆዴ አለቅሼ እባክናለው።

ለሚስቴ  ደስታ መሆን እንኳን አልቻልኩም ፤ በእኔ ሀዘን ውስጥ ድንኳኗን ጣለች እኮ ሚስትነት ከእዚህ በላይ ምን ትርጉሙ አለው። አለሁልህ አንድ ዳቦ በልተን እናድራለን መብራት ብናጣ በጨለማ ውስጥ በፍቅራችን ብርሃን እንኖራለን ትለኛለች።

የማማ ሞት አይደል ለዚ ያበቃኝ? ታድያ በቅጡ እናቴን ቀብሬ መርሳት ያልቻልኩኝ ሰው እርሱ እንዴት እንዲ አይሁን ፤ በጉጉት ሲጠብቃቻው የነበሩት እናቱን እና እህቱን በሞት ተነጥቆ እንባዬን መገደብ አልቻልኩም ፤ ያ ወጣት እያወራ ርቆ ሂዶዋል እኔ ግን የእናቴን ሞት የሚስቴን ጭንቀት አስታውሼ መንገዱ ዳር ላይ ቆሜ ድምፄን ከፍ አድርጌ ማልቀሱን ተያያዝኩት ፤ ማማ ናፈቀችኝ " ሁሉም የእናቱን ሞት በልቡ ውስጥ አመድ እንደሸፈነው ፍም በውስጡ ይነድና ቆስቋሽ ሲያገኝ ከፍ ብሎ ይሰማል። የእናቴ አሟሟት ለእኔም ግራ ነው ፤ ለማማ መድኃኒት ልግዛ ወጥቼ ስመለስ ነበር ፊቷን ሸፍነው ከህክምና መስጫ ክፍል ሲያወጧት የደረስኩት ፤ ከዛ ቡኃላ የሆነውን አላውቅም ብቻ ከሰመመኔ ስባንን እና የእናቴን ሞት በደንብ ስረዳ ግንባሯን ልስም ፊቷ የቀረብኩት ፤ ጨካኝ ነኝ እኔ!!!  እናቴን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመሰናበት ፊቷ የቀረብኩ ጨካኝ  ሞት ያኔ ተሞኘ ሞት ያኔ ክፉ ተመኘ ፤ አዎ እናትን ማጣት ህመሙ ከባድ ነው ከዚህ ቡኃላ የዝናቡ መምጣት አሳስቦት ጃኬት ደርብ የሚለኝ ሰው አይኖርም ፣ ሀዘኔን ከእኔ በላይ የሚሰማት ሚስኪኗ እናቴ የለችም ፤  እህህህህ ያማል!   ይሄ ሁሉ ቢሆንም እናቴን አስታምሜ ቀብርያለው እርሱ ግን እናቱና እህቱ በደም ተሸፍነው ነው የደረሰው። ያ ወጣት ሄዶዋል እኔ ግን ትዝታዬን ታቅፌ ህመሜን አስታውሼ ከዕንባ ከረጢት የቋጠርኩትን ፈትቼ እያለቅስኩኝ ወደ ሀኪም ቤት ቀጠሮ ተጓዝኩኝ።


ሀኪም ቤት ስደርስ አህላምዬ ቀድማኝ ደርሳ ወረፋ ይዛ ስለነበር ወደ ሀኪሙ ገባን ፤ አስፈላጊውን የምርመራ ሂደት ጨርሰን ውጤት ለቀጣዩ ቀን ተቀጥረን ፤ ተመለስን እየሄድን መንገድ ላይ ያጋጠመኝን ሁናቴ ነግርያት በጣም አዘነች ደጋግማ እያየችኝን እጄን ትስመኛለች  አፈቅርሃለው የኔ ባል ከፊታችን ካለው መከራና ችግር በላይ አፈቅርሃለው ፤ አንተ ስትኖር ነው የእኔ ጌጤ እራስህን ጠብቅልኝ እሺ አለችኝ።


እኔም  አህላምዬ ከማንም በላይ አፈቅርሻለው ፤ ግን  ማብድ መስሎሽ ነዋ ደጋግመሽ በፍርሃት ዓይን የምትመለከቺኝ ብዬ ሳቄን ለቀቅኩት በእጇ ቆንጠጥ አድርጋ ባባ !! ከዚህ ቡኃላ እንደዚህ ዓይነት ቀልድ አትቀልድ ዋ!! ብላኝ ፊቷን አዙራ አለቀሰችኝ ፤ እኔም ከቀልዴ መለስ ብዬ አፅናንቼ ግንባሯን ሳምኳት።

ልቤን  ፍርሃት ፍርሃት እያለው ነው ፤ ልጅ ያለመውለዳችን ምክንያት እኔ ከሆንኩኝ የጥፋተኝነት ስሜት ሲሰማኝ ልኖር ነው ብዬ ሰግቻለው። አዎ የአላህ ስራ ነው ቢሆንም ግን እኮ ህመም አለው ያቺ በክፍለ ዘመኑ ወደር የማይገኝላት ሚስት ምትኳን ማፍራት በእኔ ምክንያት ሳትችል ቀርታ ማየት እንዴት አያምም።

ችግሩ የእርሷም ከሆነ ከእኔ በላይ ልትጐዳ እንደምትችል እና ተስፋ የመቁረጥ ስሜት እንደሚሰማት ተረድቻለው ፤ ብቻ ይጨንቃል አላውቅም ውጤቱ ምን እንደሚሆን በጭንቀት ቀኑ አልፎ ምሽቱ ተተካ ፤ ፍንድቅድቅነቷ ዛሬም አለ እንደ ሁሌም ግሩም እራቷን አቅርባ በልተን ተቃቅፈን ተኛን። 


ደግሞ ነጋ ነግቶም አላበቃም የህክምናችን ቀጠሮ ሰዓት ደረሰ ፤ የመጀመሪያዎቹ ውጤቶች ተጠሩ ቀጣይ ተረኛ ልፎ ሰዒድ እና ወይዘሮ አህላም? አለ ከውስጥ አንድ የዶክተሩ ረዳት ፍርሃት ፍርሃት እያለኝ ወደ ውስጥ ተራመድኩኝ አህላም ፊት ላይ የጭንቀት ምልክት ይታያል።


ክፍል አስራ ስምንት ይቀጥላል ....... .......

@fonkabcha1
@fonkabcha1
265 viewsPassenger, 12:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 15:37:45 ​​ሴትን አላምንም

ክፍል 16



ሽማግሌዎቹ የአንድ አካባቢ ሰዎች ስለሆኑና በአካባቢያቸው ትልቅ ሰው ስለሞተ ነበር በአንድ የስልክ ጥሪ ኒካሁን በሙሽሮች መግቢያ ሰዓት እናድርገው ብለው በአንደኛው ሽማግሌ በኩል ለእኔ ሽማግሌዎች መልዕክት ያስተላለፉት።

ይገርማል ሕይወት ጉራማይሌ ነች ፤ በአንዱ ቤት የድግስ  ድንኳን ተጥሎ ሌላኛው ቤት ደግሞ የለቅሶ ዳስ ሁለት ዓይነት ሙሾ ሁለቱም ለእኔ ያድርገው መልዕክት አንደኛው ለእኔ ያድርገው ሞቱን ሁለተኛውም ለእኔ ያድርገው ሰርጉን ነው።


የእውነት መንገድ ለመጀመር ከሚዜዎቼ ጋር ጉዞ ጀመረናል ፤ በመዋደድ እና በፍቅር ጥላ ውስጥ ተጠልሎ የቆዬው ፍቅር ጐጆውን ሊቀለስ ውጥኑን አሳክቷል የደስታ ሲቃ ፣ የአሸናፊነት መንፈስን ተላበስኩኝ።


አዎ አህላምዬ እናቴ እና የእናቴ ምትክ ነች ፣ ለእናቴም እንደ ልጅ ሁና ፍቅርን የቸረች ሚስት ዛሬ በህይወቴ መስመር ገብታ ቃልኪዳን ልንጋባ በእምነት መስመር ልንታጠር ፣ ልብሷ ልሆን ገመናዋን ልሸፍን አህላምዬ ጋር እየሄድኩኝ ነው ፤ ወንድሟ ባለኝ መሰረት በሱፍ ተውቤና ተሽቀርቅሬ
እውነተኛ ሳቅ እና ደስታ ውስጤ ሲፀርስ እየተሰማኝ ሄድኩኝ።

የማለዳ ሃሳቤ እና የህይወቴ አጋር አህላምዬ ጋር ቤቷ ደጃፍ ደረስኩኝ። አናስገባም ሰርገኛ የሚመስል ጭንቅንቅ ሙሸራ ሳይሆን ንጉስ የሆንኩ መሰለኝ ፤ ሁሉም እኔን ለማየት የጓጓ ይመስላል በመኪናው ዙሪያ ሰዎች በእኔ ማግባት ደስታ መንዙማ እያሉ ማጀብ ጀምረዋል ፤ ፈገግ የሚያስኝ ግጥም ከመሀከላቸው ይሰማል።

ያገባም አገባ ያላገባም ያግባ
ማሜ ብቻ ቀረ ሻወር እየገባ

ማሜ ከእኔ በላይ ደስተኛ ሁንዋል የጓደኝነት ትርጉም የገባው ንፁህ እና መልካም ሰው።

 "እውነተኛ ጓደኝነት ማለት በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የማይሻክር  በመከራ ጊዜ ጥሎ የማይሸሽ ፤ እውነተኛ ጓደኝነት ማለት በመከራም ሆነ በደስታ ጊዜ የማይሻክር ፣ እንደ አለት የጠነከረ፣ በማንኛውም ጊዜ መተሳሰብና መከባበር ያለበት ትልቅ ቁምነገር ነው።

ይህንን ትልቅ ነገር ደግሞ በስርዓት እና በአግባቡ መያዝ  ትልቅ ብልህነት ነው ፤ አዋቂ ከሚያስብሉ መንገዶችም ዋናው እና አንደኛው በዚህ በመከራ በደስታ ጊዜን አብሮ መሆን ነው ብዬ አምናለሁ ።

 ጓአደኛዬም መከታ ሁኖ እንደ ወንድም ወገቡን አስሮ እንደ ሚዜ ወጌን ሊያሳየኝ ከእኔ በላይ ደክሞ ነው ውጥናችን የተሳካው። የአህላምን ወንድም ጉልበት ስሜ የአክስቶቿን ምርቃት ተቀብዬ አህላም ወደ አለችበት ክፍል አመራሁ ።


የእኔ ውብ ከጨርቃ በላይ ደምቃ በነጭ ቬሎዋ አሸብርቃ የእኔን መምጣት ትጠባበቃለች ፤ ብርሃን ፈነጠቀልኝ ገና እስከዛሬ ድረስ ተደብቆኝ የነበረው ጀምበሬ ወጣ ህልሜም ተፈታ ።

ሰዎች ስለእርሷ ቢጠይቁኝ መልሴ ብዙ ነው ፤ እርሷን በምን አየሀት ተመኘኃት ቢሉኝ በቤተሰቧ እንደምትወደድ ፣ ሰው አክባሪ ናት ብዬ ለመመስከር ከእኔ ቀድሞ የሚገኝ ያለ አይመስለኝም ።


ግንባሯን ስሜ ፣ የቃልኪዳን ቀለበቷን አስሬ ወደቤታችን በደስታ ተመለስን የእውነት መንገድ ተጀምረ ፤ የትዳር ጐጆአችን ተቀለስ ደስ የሚሉ ሁለት ዓመታት በፍቅር አለፉ። 

በትዳር ህይወታችን የመጀመሪያዎቹ ዓመታት በፍቅርና በደስታ አልፈዋል ፤ 2ተኛ ዓመት ላይ ከባድ የህይወት ፈተና አጋጠመን ማሚ በጠና ታማ አረፈች የሱቅ ስራ እየተበላሸ መጣ።

"በትካዜ እና በጭንቀት ኳተንኩኝ ፤ አህላምዬ ከምን ጊዜውም በላይ የሚስትነት ፍቅሯን እየቸረቸ ታበረታኝ እኔ አለሁህ ትለኝ ነበር።

በመኃከላችን ልጅ ባለመኖሩ ቢከፋኝም አንድም ቀን ሂደን ችግራችንን እንመርመር ብያት አላውቅም ፤ አንድ ቀን ግን አህላምዬ ቤት ስገባ ጠብቃ ሰዒዲዬ ዛሬ ማውራት ያለብን ነገር አለ ብላ ጠራችኝ ፤ ያ ሁልግዜም እንደ ፀሀይ ፈክቶ የሚታየው ፈገግታዋ ዛሬ ደፍርሷል ፣ ውብ አይኖቿ ተስፋ የመቁረጥ ስሜት ይታይባቸዋል ፤ ቢሆንም ግን ፍቅሯ ከመቀነስ ይልቅ ጨምሮ ሁሌም ድካሜን ማቅለያ ጭንቀቴን መርሻ ሁና ደስተኛ አድርጋኛለች።

ሰዒድዬ " የኔ ውድ ባል ማሚ ከሞተች ቡኃላ ተስፋ የመቁረጥ ነገር እያየሁብህ ነው ፤ አንተ እኮ ጠንከራ እና የመከራ አለት የማይፈረካክስህ ለሰዎች የችግር አቅላይ ሰው ነበርክ ፤
ታድያ ዛሬ ያ ወኔህ ያ አልረታም ባይነትህ የት ገባ  የመኖሬ ምክንያት ፣ የህይወቴ አጋሬ ፣ የእህቴ ምትክ ሁነህ ለእዚህ አብቅተህኝ ዛሬ ግን ያ ከማንም በላይ የምወደው እና የማውቀው ባሌ አልመስል ብለህኝ ሳዝን እና ስከፋ ቆይቻለው።

የኔ ውድ በደረሰብህ ሀዘን ይሄ ሁሉ ጊዜ  መብከንከኑን ተወት አድርግና ኃይልህ ሳይባክን ለትላልቅ  እንደዚሁም ዋጋቸው ከፍ ላለ ጉዳዮች ቆጥበው ፤ የሚያዳክምህ ከፊት ለፊትህ የተገተረው ግዙፍ ተራራ ሳይኾን ጫማህ ውስጥ የተሰነቀሩ ደቃቅ ጠጠሮች ናቸው ፤ የኔ ፍቅር በጊዜ ውስጥ ትናንት የትዝታ ፣ ነገ ደግሞ የተስፋ ጎተራ ናቸው ፤  ካመለጠ ትናንት....ያልመጣ ነገ ይሻላል ፤ በእጅ ያለ ዛሬ ግን ከሁሉም ይበልጣል። ዛሬ ሁሌም ያለ እየመሰለ የማይደገም ተመልሶ የማይመጣ ለአንድ አፍታ ለቅፅበት ታይቶ ዳርቻ ከሌለው የዘላለም ጠፈር ገብቶ የሚሰወር በትናንትና እና በነገ መኃል የተሰነቀረ ዕንቁ ነው። የዛሬ ሚስጢሩ እና ጉልበቱ ያለው ደግሞ "አሁን" ነው። "ቅድም" እና "ቡኃላ" ግን ያለ ቦታቸው ዛሬ ውስጥ የተደነቀሩ የትናንትና እና የነገ ሽርፍራፊዎች ናቸው። ካመለጠ ትናንት ያልመጣ ነገ ይሻላል ፤ በእጅ ያለ ዛሬ ግን ከሁሉም ይበልጣል። ውዴ ነገአችንን እናስተካክለን ዛሬያችን እናሳምር ዳግም ጠንክረን ወደ ስራ እንመለስ።

ሌላው ደግሞ ውዴ እየፈራንም ያላወራንበት የልጅ ጉዳይ ብናነሳው ጥሩ ነው ፤ ልጅ እንደምትወድ አውቃለው ሀዘንህም የዚህን ያህል የበረታው ማሚ የአንተን ልጅ ሳታይ መሞቷም ጭምር ነው ፤ የኔ ውድ ምን ትላለህ ነገ ሂደን ብንመረመር አለችኝ። አዎ ልጅ እወዳለው ግን የአህላምዬ ይበልጣል ፤ መንገድ ላይ ያገኝችው ልጅ ሁሉ የእርሷ እየመሰላት አቅፋ ትስማለች ወደእኔ ዞር ብላ እንደዚህ ቆንጆ ልጅ እንወልዳለና? ስትለኝ ሁሌም ፈገግ ብዬ በሚገባ ነበር ምላት።

 አሁን ግን ሁለት ዓመት አልፎን  ወደ ሶስተኛ ዓመት ልንሸጋገር ጥቂት ነው የቀረን ፤ እኔም በሀሳቧ ተስማምቼ እሺ ብያት መሽቶ ስለነበር ወደ መኝታችን አመራን። አይነጋ የለ ነግቶ በቀጠሮዋችን መሰረት ወደ ሀኪም ቤት ለመሄድ መንገድ ጀመርን።

የእኔ ህይወት ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ዳክሯል ፤ ያሳለፍኳቸውን አስቀያሚ የህይወት ጉዞዎቼን ያኖርኩባት ትንሿ ዲያሪዬ የበዛ ሀዘን እርሷ ላይ ከመፃፏ የተነሳ ያለ ገደብ ባለቀሰች ምኞቷ ነበር።  ሀበሻ  የሀዘን ታሪክ ይወዳል ሀዘኔን በመፅሀፍ ላሳትመው እንዴ እያልኩ ለሳቅ የማይሆን ቀልድ መቀለድ ከጀመርኩኝ ሰነባብቻለው ፤ ድንገት አንዳች  ድምፅ ከሄድኩበት ሀሳብ መለሰኝ። አንድ ልቡ ጠርቶ ልብሱ የጎደፈው ፣ እጁ ላይ ማንም ሊያያቸው የማይፈቅዳቸው ሁለት ፎቶዎች በደረቱ ይዞ "ሴት አላምንም፣ሴት አላምንም" እያለ መንገድ ላይ የሚበጠብጥ ወጣት ከንቱ ከሆነው ቀልዴ አባነነኝ። ከእርሱ ድምፁ ጋር ህፃናቶችም "ሴት አላምንም መጣህ እያሉ ያበሽቁታል" ፎቶዎቹ ግን እነዛ ፎቶዎች ውስጥ ማን እንዳለ ማወቅ ፈለግኩኝ ረዝም ሰአት ሃሳቤን ወሰደው ከቅርብ ርቀት ላይ ስለ ነበር ለማየት አልተቸገርኩም ደነገጥኩኝ ከመቼው በላይ የማይረሳኝ የፊት ገፅታ ግን እንደዚህ እንዴት ሆነ አዎ እራሱ ነው....


ይቀጥላል.... 17


@fonkabcha1
@fonkabcha1
211 viewsPassenger, 12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 21:55:25 ​​"ሴትን አላምንም"

ክፍል 15

በእህቴ ጉዳይ እንደ ወንድም ላወራህ ነበር ፤ እውነት ለመናገር ስለ አንተ ምንም ሳላውቅ ነበር አጐትህ ሀጅ በሽር "ልጅህን ለልጄ" ብለው ወደ ቤት የመጡት ፤ ሀጂ በሽር ሀገር ምድሩ የሚያውቃቸው የተከበሩ የታፈሩ የታወቁ ትልቅ ሰው ናቸው ፤ ከእርሳቸው ጋር መዛመድ ምን ያህል ትልቅ ዕድል እነደሆነ ለእኔና ለአባቴ ቤተሰቦች እንዲሁም እርሳቸውን ለሚያቁ ነው የሚገባቸው። ግን ነገሩን ማጤን ስለፈለግኩኝ የአጭር ቀን ቀጠሮ ሰጥቼ አንተን መከታተል ነበረብኝ ፤ እውነት አህላም ወዳህ ሊሆን ይችላል ደግሞ ወዳሀለች ፍቅር እውር ነው ለመውደድ ጥቂት .....

ለተወሰኑ ደቂቃዎች የአህመድን ስሜት መረዳት አልቻልኩም ፤ ሰፋፊ ሀሳቦች እያነሳ ስለ ፍቅር ብዙ አወራኝ ፤ አንዳች ጥርጣሬ ይሰማኝ ጀመር አህላምን ሊከለክለኝ አስቧል አልያም ትንሽ ቆዩ ሊሆን ይችላል ግን ጥርጣሬ አልወድም " በጥርጣሬ ምክንያት ስንት ደጋግ ሰዎችን አጥተናል ፣ በራሳችን መጥፎ ጥርጣሬ ምክንያት እምነት ያሳደሩቡን ሰዎችን አስቀይመናል ፣ በጥርጣሬ ምክንያት ስንቱ ቤቱ ፈርሷል" የመጨረሻዋ የንግግሩ ማብቂያ ናፍቆኛል።

ሰዒድ አለ አህመድ ጉሮሮውን እያጠራረገ ዘለግ ያለ ንግግር እና የመቋጫ ንግግር ለመናገር የፈለገ በሚመስል የድምፅ ጉልበት "የህይወታችን አዲስ ንጋት የሚጀምረው የምንታገልለት ፣ የምንወድቅለት፣የምንነሳለት፣ ተስፋ የማንቆርጥበት ዓላማ ሲኖረን ነው የኔ የህይወቴ አዲስ ንጋት ደግሞ ቤተሰቦቼ ናቸው። ከዛ ውሰጥ ደግሞ አህላምዬ የአንበሳውን ድርሻ ትይዛለች ፤ እህቴ አንዲትም ቀን አስቀይማኝ አታውቅም እንደ ታላቅ ወንድም ትዕዛዜን አክብራ ፣ ሲከፋኝ አፅናንታ ፤ ጉድለቴን በእህትነት ፍቅር ሞልታ ታናሽ ሳትሆን  ታላቅ ሆና ነው እዚ ደረጃ የደረሰችው ፤ የአባታችን ጉድለት በእርሷ ፍቅር ሞልተናል እናቴም ያለእርሷ እጅ እግሯ አይሰራም ፤ የቤተሰባችን ቀኝ እጅ ለእራሷ ደስታ ሳትኖር ለቤተሰብ ፍቅር  ብላ ኑራለች።

 ስራዬን ስል ከትምህርት ቤት ወደ ቤት በመኪና ከማድረስ ውጪ  አንድም ቀን የውስጧን ስሜት ተረድቼ አላውቅም ፤ ፍላጐቷም ለብሶ መታየት ፣ ደምቆ መኖር አልነበረም ታዲያ ይህችን የቤታችንን ብርሀን ነው የጠየቅከን። 

አጐትህ አናግሮኝ ከሄደ ቡሀላ እህቴን ለማናገር ፈራ ተባ እያልኩኝ ወደ ክፍሏ ሄድኩኝ ፤ የትዳር ምርጫዋ ምን መሆን እንዳለበት ስለ ትዳር ፣ ስለ ፍቅር አውርችያት የማላውቅን ልጅ በምን መስፈርት መርጥሽው ማለት ከበደኝ ፤ በምን መስፈርት ትበለኝ መቼ ስለፍቅር ስለ ፆታዊ ፍቅር መቼ አውርችያት አውቃለው።

ደግሞም ለትዳር ምሳሌ የምሆን ሰው አይደለሁም ፤  በትዳሬ ደስተኛ አልነበርኩም ትዳሬን በትኜ ወደ እናቴ ቤት ከገባሁኝ ይህው 5 አመት ሊሞላኝ በጣት ሚቆጠሩ ቀናቶች ናቸው የቀሩት ፤ ቢሆንም ግን እንደታላቅ ወንድም ማናገር ነበረብኝ።

አህላምዬ? ልጁን ወደሽዋል? ብዬ ስጠይቃት   የመለሰችልኝ መልስ ልቤን ገዛው እረፍት ተሰማኝ  እህቴ ቀድማ እንደበሰለች ተረዳሁኝ።

" ወንድሜ ከሰዒድ  ከምንም በላይ እርጋታው እና ለሰው ያለው ክብር ነው የገዛኝ ፤ ከዛ ቡሀላ በእርሱ ተሸነፍኩኝ ከእርሱ በፊት ማንንም አፍቅሬ አላውቅም ፤ ማፍቀር ምን ማለት እንደሆነ አስረዳኝ እየዋለ እያደረ ማፍቀር ማለት ከራስ ላይ ቀንሶ ስለሰው መኖር ለሰው መጨነቅ እንደሆነ ሰዒድ አሳየኝ ፤ የራሱን ፍላጐት ትቶ ከምንም በላይ ለእኔ መኖር ችሎ አሳየኝ ።

እህታችን ሀሊማ ለእኔ ምን ያህል እንደነበረች ለአንተ አይጠፋህም ፤ ሁሌም ደስተኛ እንድሆን እና በህይወቴ እንዳልከፋ በባባ መሞት የጠለቀ ሀዘን እንዳይሰማኝ አድርጋ ነው ያሳደገችኝ ፤ እንደ እናት ሁና ነበር እርሷን ሞት ሲነጥቀኝ ከጐኔ ሁኖ ያበረታኝ እርሱ ነበር ፤ እርሱ መከታዬ እና መሸሸጋዬ ሆኖ ነው ያንን የመከራ ጊዜ ያሳለፍኩት እና ወንድሜ እርሱን ከልብ ወድጄ ፈቅጄ ነው ለእናንተ ያሳወቅኳቹ ፤ ማፍቀር ከምንም እንደሚልቅ ያስተማረኝን ሰው እንዳገባ መልካም ፍቃድህ ይሁን ብዬ እጠይቅሃለው ፤ ወንድሜ ሳልነግርህ ቅልጥ ያለ ፍቅር ውስጥ በመግባቴ ይቅርታ" ብላ ነበር የነገረችኝ ፤ ሳላይህ ወደድኩህ እርሷ እንደምትለው ዓይነት ሰው መሆንህን ለማጣራት ባደረግኩት ጥረት መልካም እና ሙሉ ስብዕና ያለው ወጣት ሆነህ አግኝቼሀለው ፤ ለእናትህ ያለህ ፍቅር ደግሞ ሚዛንህን ከፍ አደርጐታል አለኝ።

እጁን ትከሻዬ ላይ አኑሮ "እህቴን አደራ ሰጥቼሃለው  እንደ ወንድም ደግፈህ ፣ እንደጓደኛ ሚስጥሯን ተካፍለህ ፣ እንደ ባል መከታ ሆነህ አኑራት ፤ ከእኔ ያጣችውን ፍቅር ትሰጣት ዘንድ እጠይቅሃለው።  ከህይወቴ የተማርኩት ትዳር ማለት ማለፍ ነው ፤ በትዳር ውስጥ ትዕግስተኛ መሆን ግድ ነው ፤ ሴት ልጅ ደግሞ በባህሪዋ ትንሽ ነገር ያስደስታታል ትንሽ ነገር ያስከፋታል ያንን ችለህ ማለፍ የግድ ይላል ፤ ወዳሀለች ውደዳት ፣ አምናሀለች ታመንላት ፤ አንድ ሰው የመከረኝን ልንገርህ እህቴ ስለሆንች ሳይሆን ከጠቀመህ በሚል ነው።

"አንድ ሴት ልጅ የቤተሰቦቿ የ 20 ዓመት ልፋት ነች ፤ አየህ ቤተሰቦቿ ሚስትህ ትሁን ብለው ሲሰጥሁ ዋጋ የከፈሉባትን ፣ ያሰተማሯትን ፣ ዕድሜያቸውን እና ወጣትነታቸው የጨረሱባትን ልጇቸውን ነው ፤ የሚሰጡህ ታድያ ይህች የሙሉ ቤተሰቡ ልፋትና ድካም የሆነችን ልጅ በእጅህ ከገባች ቡሀላ ከመሬት ላይ እንደተገኝች ዕቃ እንዳትንቃት። ሰዎች ሴትን ልጅ ከተንከባከብካት ጭንቅላትህ ላይ ትወጣለች ብለው የሚመክሩህን አትስማ ፤ ብትወጣስ ቦታዋ እርሱ አይደል እንዴ "ሚስት ለባሏ ዘውድ ናት " የሚባለው ቦታዋ እዛ ስለሆነ ነው ፤ ንጉስ መሆን ከፈለግክ ሚስትህን አንግሳት ብለው የመከሩኝን መቼም አልረሳም ይህን መልዕክት ልብህ ላይ አኑረው ብሎኝ ተነሳ ። "ቤተሰብ በመሆናችን ደስተኛ ነኝ በተባለው መሰረት የሚቀጥለው ሳምንት እሁድ ሰርጋቹ ይፈፀማል ፤ ከቤተሰብህ ጋር ሁሉንም አውርተናል እናንተ አትጨነቁ የራሳቹን ነገር አሟሉ ፤ ከዚህ ቡሀላ የማይህ በሙሉ ልብስ የሰርጉ ቀን ይሆናል ። እንኳን ወደ ቤተሰባችን ተቀላቀልክ ብሎኝ ፈገግ ብሎ አቀፈኝ።

"እኔም አመሰግናለው የእናንተ የቤተሰብ አባል ስለሆንኩኝ ክብር ይሰማኛል ፤ ለሁሉም ቃል የለኝም አደራህን ተረክቤ በደስታ ለማኖር ቃል እገባለው ፤ አህላም ለእኔ የዘመናት ውጥኔ እና ምኞቴ ናት ፤ አልሃምዱሊላህ ዛሬ በፍቃደኝነት እርሷን ስለሰጠህኝ ከባድ ሃላፍትና እንደሰጠህኝ እረዳለው አደራዬንም በምችለው ልክ እወጣለው" አልኩት።

ከልብ የመነጨ ሰላምታችንን ተለዋወጥን ወደ መኪናችን ሄድን ፤ ታላቅ እረፍት ተሰማኝ ያሰብኩት ተሳካ፣ህልሜም ተፈታ፣ ድፍርስ መስሎ የታየኝ የወንድሟ ሃሳብ ጠራ ፤ የተመኘሗት አህላም በእጄ ገባች ፤ ታላቅ የአሸናፊነት ስሜት በምድር ላይ ከእኔ በላይ ማን ዕድለኛ አለ የወደዳትን የተመኛትን ያገኘ  አግኝቶም ሊያጋባ ጥቂት ቀናቶችን የቀረው እኔ ብቻ ነኝ።

ማሳካት ያለብን ነገር ሁሉ አሳካን አህላምዬ የቤት ዕቃ በመግዛት bussy ስለሆነች በስልክ ብቻ ነበር የምንገናኛው ፤  ህልማችን ዕውን የሚሆንበት ቀን ደረሰ ፤ ሁሉ ቤተሰብ በእኔ ሰርግ bussy ሆነዋል ፤ ሽማግሌዎች በጠዋቱ ኒካህ ሊያስሩ እየሄዱ መንገድ ላይ አንድ የስልክ ጥሪ አስቆማቸው....


ይቀጥላል……… 16

@fonkabcha1
@fonkabcha1
248 viewsPassenger, 18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 21:54:12 ​​​​​​​​​​​​​​


"ሴትን አላምንም"

ክፍል 14

ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ


ከጠዋት ጀምሮ አህላምዬን አላገኝሗትም ፤ ስልክም አልደወለችም ናፍቃኛለች ፤ ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ሆኜ እርሷን ሳስብ ግን አዲስ ንጋት እና  አዲስ ተስፋ ይታየኛል ፤ ሀገሬ ስትጎዳ አህላምዬም የምትጐዳ ስለሚመስለኝ እጨነቃለው።

ሁሉም ቤት የራሱ ሀዘን አለው ፤ የዛሬው አደጋ አህላምዬ ላይ ቢሆንስ? አንዳች መራራ ነገር እንደቀመሰ ፣ ተፈጥሮ የማያውቅ አስቃያሚ ነገር እንደተመለከት ፣ ታይቶ የማይታወቅ አደጋ እንዳስተዋለ ሰው ዘገነነኝ።

አህላምዬ ሆና ቢሆን ኖሮ የመኖር ተስፋዬ ጨልሞ መንገድ ላይ ስኳትን ታሰበኝ ፤  ግን አህላም አይደለችም ፤ ልጁ ግን የራሱ አህላሞች በጥቅመኛ ባልስልጣናቶች ራስ ወዳድነት አጥቷል።  ሁሉም የሚወደውን ሰው ሲያጣ ከአካሉ ላይ ግማሹ እንደተወሰደ ይታመማል ፤ ስንቱ የወደደውን ተነጠቀ? ስንቱ ያፈቀረውን ተቀማ? የእኔ አህላም ግን አሁንም ከእኔ ጋር ነች ፤ ታድያ አህላም ደህና እንድትሆን ሀገሬ ደህና መሆን የለባትም?

 
ለእዚህ ነው ጃርት ሁነው ሀገራችን ያሸበቷትን ጥቅመኛ ባለስልጣኖች ፣ ጐርሰውባት እጇን የነከሷትን ሹማምንቶች ከልብ መስደቤ አዎ ሙስኞች !!! ናቸው።

 ስለምንወዳቸው ደስታ ስንል መልካምን መስራት እንዳለብን ያለተማርን ከንቱ ትውልዶች በሰፈሩት ቁና መሰፈር እንዳለ ረስተን በሰዎች ቤት የሀዘን ዳስ ጥለን እኛ ግን እንጨፍራለን ፤ እቤትህ ብዙ አህላሞች አሉህ እህቱን እና እናቱን ነጥቀህ ያንተን አህላሞች የሚተዋቸው ከመሰለህ ተሳስተሃል።
የመኪናዬ መስታወት ጋር  አንዲት ህፃን ልጅ መጥታ ስትቆም ከሃሰቤ ባነንኩኝ ፤ እጇን ወደ አፏ አስጠግታ ዳቦ ግዛልኝ የምትል ትመስላለች ፤ ገላዋ የቆሸሸ ፣አካሏ የዛለ፣ ገፇ የተጐሳቀል ሚስኪን እናቷ ከመንገድ ዳር ሁና ነይ እያለች ትጠራታለች። የመኪናዬን መስኮት ከፍቼ ያለችኝን ብር ሰጥችያት ወደ እናትሽ ፈጥነሽ ሂጅ ብየ ላኳት ፤ እናቷ እንደዚህ የመሆኗ ሰበብ ምን እንደሆነ ባላውቅም ብዙዎቹ ሴቶች ወደድኩሽ አፈቀርኩሽ በሚሏቸው ወንዶች ጭልጥ ያለ ፍቅር ውስጥ ገብተው በምትፈፀመው የአንዲት ቀን ስህተት ነው። "ሴት ልጅ ለፍቅሯ እራሷን አሳልፋ ትሰጣለች" ለሚወዳት ወንድ ክብሯን አሳልፋ መስጠት ትንሹ ስጦታዋ ነው ፣ አዎ ሴት ልጅ ህይወቷን ትሰጣለች ፣ በጥላዋ ስር የምታፈቅረውን ሰው ታኖራለች ፣ ከሀዘንህ ውስጥ ሳቅህን ፈልቅቃ ትቸርሃለች ምን አልባት በጥላዋ ያስጠለለችው ፣ ክብሯን አሳልፋ የሰጠችው ወንድ ከልጇ ጋር ሜዳ ላይ ጥልዋት ሄዶ ይሆናል። 

አህላምዬ ባለመደወሏ መረጋገት አልቻልኩም ፤ ስልኳም አይነሳም በሀሳብ ተወጥሬ በፍጥነት እየነዳሁኝ ነው። የአህላም ስልክ አለማንሳት ፣ የአጐቴ ደጋግሞ መደወል ፣ የወንድሟ በይበልጥ እኔን መፈለግ ሁሉም አሳሳቢ ነው ። አህላምዬ ደወለች ነግቶ እስከማያት የምነፍቃት ልጅ ዛሬ ቀን ሙሉ አለመደወሏ አናዶኛል ፤ ፍቅር አንድ አንዴ አመልህን ያሳጣሃል ያነጫንጭሃል ፤ ቀኑን ሙሉ ያልደወለችው በምክንያት ሊሆን እንደሚችል ቢገባኝም ግን ከፍቶኛል ፤ ከምንም በላይ የሚያስፈልገኝ ፈዋሽ ድምፇን ዛሬ ለመስማት አልታደልኩም ነበር።

በአኮረፈ ድምፅ ስልኬን አነሳሁኝ የኔ ውድ ባል? የመጀመሪያው ንግግሯ ነበር  ሳቄን መቆጣጠር አልቻልኩም ፤ ተጨንቄ ያመጣሁትን ኩርፊያ በአንዲት ቃል ናደችው ፤ ግን መሸነፍ አልፈለኩኝም አህላም! ለምንድን ነው ስልክ የማታነሺው ? ለምንድን ነው መልሼ እደውላለው ብለሽ ቴክስት የማታኖሪው?  ሰው ይጨነቃል ሰው ያስባል ለምን አትይም? ብዬ ጠይቅኳት።

ሰዒዲዬ "ስልኬን ቻርጅ ሰክቼው (class) ገብቼ ነበር ከክላስ የወጣሁት አርፍጄ ነው መደወል ነበረብኝ፣ ቴክስት መላክ ነበረብኝ ግን ጠዋት ረፍዶብኝ ስለ ነበር ቸኩዬ ነበር የወጣሁት ይቅርታ የኔ ባል? አለችኝ። እስካሁን ረጋ ብዬ ነው የምሰማው ከምክንያትዋ በላይ ያሰመነኝ ድምፇ ነው ፤ የጥፋተኝነት ስሜት ተሰምቷት በልበ ሙሉነት ይቅርታ አለች። ሰው ስለጥፋቱ ይቅርታ ቢል ዓለም ሰላም ትሆን ነበር ፤ ፈገግ ብዬ "ይህ ሁሉ ጥሞና ይሄ ሁሉ ረጋ ብሎ የማዳመጥ ብቃት ለሌላም ለሌላም ነገር ቢሆን ምን አለበት አይ ፍቅር አልኩኝ" ፤ ለሌላ ሰውማ እንዲህ በጥልቅ ተመስጦ ለመስማትና ልቤም አዕምሮዬም መች እሺ ይላሉ አይ ፍቅር ሁለመናዬ እርሷን ለምዷል።

ናፍቀሽኛል ከአሁን ቡሃላ እንዲ እንዳታደርጊ አልኳት እርሷም እሺ የኔ ባል ደህና ዋልክልኝ ግን? አለችኝ አዎ ደህና ነኝ አንድ አንድ ደስ የማይል ነገር ብዬ ቀኑን ሙሉ ያጋጠመኝን ሁሉ ነገርኳት ፤ ሆስፒታል ስላየሁት ልጅ ፣ ስለ ህፃኗ የመሀመድ አባትን ሀኪም ቤት እንደወስድናቸውም ጭምር።  በመሀል  አህላምዬ በሗላ እደውልልሻለው ብዬ ስልኬን ልዘጋው ሳቅማማ  "በቃ"? አለችኝ "አፈቅርሻለው !! የመኖሬ ምክንያት አንቺ ነሽ እራስሽን ጠብቂ አልኳት"።
የኔ ባል?  
ወዬ?
ለደቂቃ ሳጣህ ልቤን ይጨንቀኛል ስትጨርስ ደውልልኝ ፤ ከት/ቤት እስክመለስ መንገዱ አላልቅ ብሎኝ ድምፅህን እስከሰማ በናፍቆት ሙቼልህ ነበር የኔ ባል ሽልማቴ ነህ አንተም እራስህን ጠብቅ አለችኝ።

አህላም ከመደወሏ በፊት ወንድሟ የምንገናኝበት ካፌ ነግሮኝ ስለነበር ወደቦታው አመራሁኝ ፤ ከአህላምዬ ጋር የነበረኝን የስልክ ግንኙነት ያቋረጥኩት ትራፊክ ስለነበረ ነው።
 ወንድሟ ለምን በአስቸኳይ እንደፈለገኝ ባይገባኝም ወደእርሱ ጉዞ ጀምርያለው ፤ የትራፊክ መጨናነቁ መኪና መንዳት አሰልቺ አድርጎታል።  በመንገዴ ሁሉ አህላም ትዝ እያለችኝ በእርሷ መፈቀሬን እያሰብኩኝ ፈገግ እላለው ፤ እርሷ የእኔ ትናንት ነች አህላም የእኔ ነገ እና የመኖሬ ምክንያት ከሆነች ሰነባብታለች ፤ ድምፇንም ሰምቼ ትናፍቃኛለች ፤ የአህላምዬ ናፍቆት  ተራራውን አስምሶ ፣ ቁልቁለቱን አምዘግዞ የትም ቢያደረሰኝ አልፈርድበትም ምክንያቱም ተሸንፌላታለው። 

ከወንድሟ ጋር ወደ ተቀጣጠርንበት ካፌ ደርሼ መኪናዬን አቁሜ ስወርድ አንድ ሰው ከሩቅ ሰላምታ ሰጠኝ እርሱ እንደሆነ ገምቼ ወደሱ ተራመድኩኝ።

ተቀምጦም ረዥም እንደሆነ ያስታውቃል ቀይ  ዘናጭ አይነት ነው ፤ ፊቱ ላይ እርጋታ ይነበብበታል ከወንበሩ ተነስቶ እጁን ዘረጋልኝ ፤ አህላምዬን እየሰጠኝ መስሎኝ በፍጥነት እጄን እጁ ላይ አኖርኩት ፤ "አሰላሙ አለይኩም" ሰዒድ "ወአለይኩም ሰላም" አህመድ ይቅርታ? መንገድ ዝግ ሁኖብኝ ነው የዘገየሁት አልኩት።

"አብሽር መንገዱ እንደ ሚዘጋጋ ገምቼ ነበር  ከዘገየህም ብዬ ይህችን መፅሀፍ ለማንበብ ሰዓት አገኛለው ብዬ ይዣት ነበር"
ስራ እንዴት ነው?
ቤት ሰላም?
እናትህ እንዴት ናት? የተደራረቡ ጥያቄዎችን ጠየቀኝ እኔም በእርጋት ሁሉንም መልስኩኝ።

ግን ለምን እነደፈለገኝ ነግሮ አይገላግለኝም ? ጨንቆኛል ሰውነቴ ላብ አጥለቅልቆታል መጨነቄ ፊቴ ላይ እንዳያስታውቅ የቻልኩትን ጥረት እያደረግኩኝ ነው።
ሰዒድ "ዛሬ የፈለግኩህ ....


ክፍል አስራ አምስት ይቀጥላል.......

@fonkabcha1
@fonkabcha1
234 viewsPassenger, 18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 22:29:57 ​​​​​​​​​​​


ሴትን አላምንም

ክፍል 13

ሆስፒታሉ በታማሚዎች ተጨናንቋል ፤ በዕለቱ  40 ሰዎችን ይዞ ሲጓዝ የነበረው የህዝብ ማመላለሻ  አውቶብስ ከተማ መውጫ ላይ በደረሰበት አደጋ   ሆስፒታሉ በለቅሶ እና በሁካታ ተሞልቷዋል የጓደኛዬ መሀመድ አባት ቀጠሮ ስለነበራቸው ነበር በጠዋቱ እኔና መሀመድ ሆስፒታል ይዘናቸው የሄድነው።

በደረሰው አደጋ ቤተሰቦቻቸውን ያጡ ሰዎች በሀዘን ተኮማትረው ሳይ ከቦታው መንቀሳቀስ አልቻልኩም አንድ ድምፅ ውስጤን ረበሸው ወይኔ " እናቴ" ወይኔ " እህቴ" ይላል… ድምፁን ወደሰማሁበት አቅጣጫ ስዞር አንድ እድሜው ወደ 25 ዓመት ገደማ የሚሆን  ወጣት የደረሰበትን ሀዘን መቀበል ከብዶት ለያዥ ለገናዥ አስቸግሮ ያለቅሳል " እመጣለው ብላቹ ዋሻቹህኝ ፣ ደርሻለው ብላችሁ ካዳቹህኝ" እሺ ማን አለኝ እናቴ? አንቺም ጨከንሽ? …… ምን ዓይነት ልብ የሚሰብር ሀዘን ነው?  እናቱንም እህቱንም ነው በመኪናው አደጋ ያጣው።  ከምንም በላይ የአደጋው ምክንያት ልብን ይሰብራል ፤ በመንገድ ብልሽት መኪናው ተገልብጦ… …… ዜናቸው ይገርምሃል በሰጠሃቸው ገንዘብ ደስታህን ሳይሆን አሟሟትህን አሳምረው ይነግሩልሃል…… ለእነሱ በሰማይ ላይ መንገድ አመቻችተው ለሰማዩ ጉዞ መሳካት ከመሬትህ እና ከመንገድህ ላይ ይሰርቁሃል ሻማ ነጋዴዎች አዎ ሻማ ነጋዴዎች ናቸው እነዚህ ምርታቸውን ለመሸጥ የሰዎችን ጨለማ የሚጠብቁ  ሻማ አምራቾች ፤ መቼም ቢሆን የብርሃን መኖርን ለእነሱ አያስደስታቻውም ጨለማ ነው የመኖር ምክንያታቸው  ……… ለእነዚህ ጥቅመኛ ባለስልጣናት ሞትህ ለእነሱ ድግስ ነው በጥገና ሰበብ ለመንገዱ በጀት ይፀድቅላቸዋል… … ለእነሱ ሀዘን ማለት በውስኪ አለመራጨት በገንዘብ ላይ አለመረማመድ እንጂ የእናት ሞት አይደለም……  በምላስ ጫፍ ላይ የመዳን እና የመሞት ሁኔታ ላይ ለወደቀ ሰው የሚሰነዘር የማበረታቻ ቃል በእርግጥም ከወድቀት ለመነሳት እና ከችግሩ ለመውጣት ያስችለዋል። አፍራሽ ቃል ደግሞ የወደቀን ሰው ዳግም እንዳይነሳ ሊያደርገው ይችላል። ስለዚህ ለእዚህ ህልሙ ለጨለመበት ፣ ልቡ ለተሰበረው  ወጣት ምን ዓይነት ገንቢ ቃል ከአንደበቴ ይውጣ በርታ ልበለው? የሞተቸው እኮ እናቱ ነች።

እናት እኮ እንኩዋን ለዘለዓለም ከሞት መንገድ ገብታ ለአንዳአፍታ እንኳን  ከቤት የጠፋች ዕለት አይደለም ሰፈሩ ሀገሩ ጭር ይላል ቀኑ ይጨልማል ፣ የቤት ወና መሆን በእናት አለመኖር ውስጥ ይከሰታል ፣ ዓለሙ ይጨነቃል እንኩዋን ሙታ አይደለም በመኖሯ ውስጥ ያጋጠማት የራስ ምታት እንቅልፍን ይነሳል… የእናት ሞት ህመሙ ጥልቅ ነው እነዚህ ገንዘብ ያሰከራቸው ፣ የስልጣን ጥም የሰው ደም ያስጐነጫቸው ፣ ከንቱ ሹማምንት የአደጋው ምክንያት የመንገድ ብልሽት ነው ይላሉ  ፤ የተበላሸውስ "አዕምሮዋቸው" የተበላሸውስ ስብዕናቸው ነው።  ሰው ሰው የሚሆነው ስለ ሰው ሲያስብ እና ሲጨነቅ ነው ፤ በእናትህ እና እህትህ ሞት ዳስ ጥለው መደገስ የሚፈልጉ  የመንገዱን በጀት በልተው የልጁን እናት እና እህት ቀጠፉበት ፤  ታድያ እንዴት ንፁህ ትውልድ ይውጣ በቂም በቀል ያደገ ትውልድ እናቱን ገድለው እንዴትስ ስለ ሀገር ፍቅር ይኑር፣ ሀገሩ እናቱን ገድላበት። የህይወት ጣዕሙን ፣ የኑሮ ቅመሙን ሁሉ ወስደውበት እርሷ በሌለችበት ዓለም  እንዴት  መኖር ያስችለዋል ፣ መኖር የማይሉት ሕይወት መቆሚያ የሌለበት የመከራ መንገድ ታድያ ከቶ እንዴት ይራመዳል ፤ እናቱ ባፀናችው ምድር እርሷ በሌለችበት ዓለም እንዴት ቆሜ መሄድን ይችላል ፤ ህልሙን ሰርቀው በባዶ አስቀሩት መከታ የሆነችውን እህቱንም ነጠቁት ፤ ስለ እህት ምን ያውቃሉ! እንቅልፋቸውን የሰው ደም አጨናግፎባቸው ፣ ፍራሻቸው በሰዎች በደል እና ግፍ ምቾቱ ተገፎ ለእነርሱ ሰው ምንድን ነው አይደለም ሰው እናትስ ምንድን ነች።

መሞታቸው ለዚህ ወጣት ከመርዶም መርዶ ሁኖ ሀዘኑን መቋቋም አልቻለም በእናቱ እግር ላይ ተኝቶ ያደገው ወጣት መሬት ላይ አንገቱን አሳረፈ ፣ ውሉ ሁሉ ጠፍቶበት አቅሙን አሳጥቶት ሀኪም ቤቱ ደጅ ላይ ሲኳትን ዋለ አሁን ነው ከሰው መሀል ሁኜ ሰው ይናፍቀኛል ወግ…  ዙሪያውን ሰው ከቦታል ፤ ግን እናቱ የለችም ፤ ያቺ ሚስጥረኛ እና መከታ የሆነችው እህቱ እስትንፋሷ ተቋርጦ ነፍሷ ከአካሏ ተነጥሎ በድን ሁናለች።

የዚህን ጊዜ ነው እንጂ ቅኝትን መቀኝት

ሞትን ሞት ይውሰደው
ከእኔ ወሰደብኝ
ባዶዬን አስቀረኝ
እናቴን ነጠቀኝ
እህቴንም ቀማኝ
ሞትን ሞት ይውሰደው
የሚለውን ግጥም  ለእዚህ ወጣት መስጠት

ላይጨረሱ ይጀምራሉ ፣ ላይጀምሩ ቃል ይገባሉ ሰው ሲሞት ተሰብስበው የሀዘን  መግለጫ ይሰጣሉ ፤ ህልሙን ቀብረው የምን መግለጫ ነው የእናት ሞት ያልገባቸው ተወልደው የመከኑ ሀገርን ሽጠው በሸጡት ሀገር ለመኖር ልብ ይሰብራል የእናቱን እና የእህቱን አስክሬን ከሬሳ ክፍል የልጁ ዘመዶች አወጡት… … አልቻለም እራሱን ስቶ ወደቀ ሰዎች ተረባርበው ወደ ህክምና መስጫ ክፍል ወሰዱት ሙሾ አውራጆቹም ፣ ዘመድ አዝማዶቹም ሕይወታቸውን ይቀጥላሉ እርሱስ ከህክምና ወጥቶ የት ሊሄድ ነው ? የእናቱስ ምትክ ማን ይሆን? መራቡን አውቃ የምታበላው ፣ መጠማቱን አውቃ የምታጠጣው እናት ከየት ትመጣለች ? ትዝታውን እና ናፍቆቱን ታቅፎ ይኖራል እንጂ …… እናቱን ያጣ ያውቀዋል ስቆ አለመሳቅን ይማራል ፣ ተደስቶ አለመደሰትን ይቀኛል።

እነርሱ ግን የአደጋው ምክንያት የመንገድ ብልሽት ነው ይሉሀል… … ስለ ተበላሸው ምክንያት ግን አይነግሩህም…… ለሀዘንህ በተጣለው ድንኳን ነጭ ልብሳቸውን ለብሰው ይመጡልሃል……  የተሰበሰው ሰው ከተበተነ ቡሀላ ቦታው ላይ መቆየት አልቻልኩም ዕንባ እየተናነቀኝም ቢሆን ከሆስፒታሉ ወጣሁኝ።     የድሀ ዕንባ ሲፈስ የወንዝ ውኃ የሚፈስ የሚመስላቸው ድሀ ስለ ፍትህ ሲጮህ ውሻ የሚጮህ የሚመስላቸው ባለስልጣኖች። የዛሬው የሞት አደጋ ለእነርሱ ምንም አይደለም ፤ የተሰጣቸውን ወረቀት ይዘው በአደጋው የሞቱትን ሰዎች መዘርዝር ነው የእነርሱ ስልጣን፡፡ ከሚጠቅማቸው ሰው ሞት ውጪ ንፁህ ሰው ሲሞት የወፍ ግልገል የሚሞት በሚመስላቸው ሰዎች ተከበን ነው ስለ ሀገር ለውጥ የምናወራው ፤ ጉልበት ስላላቸው በደካሞች ላይ ያሰቡትን ሁሉ የሚሠሩ ከንቱ አመራሮች ስለ ሀገር ሉዓላዊነት ያወራሉ ፤ ሀገር ማለት እኮ ሰው ነው ሰው እንዲህ ወጥቶ ከንቱ እየቀረ ስለ ምን ሀገር?

ሰውን ለማጥፋት እጅግ የሚጥሩ ሰውን ካላጠፉ እንቅልፍ የማይወስዳቸው ናቸው ሀገራችን እያስተዳደሩ ያሉት፡፡

ያማል!  እናቱን ነጥቀው ብቻውን አስቀርተውታል እህቱን ወስደው ያለ ሚስጥረኛ አሳጥተውታል ስልኬን ሳወጣው ብዙ missed call አለው ማማ ፣ አጐቴ እና አንድ ደግሞ save ያልተደረገ ስልክ save ባልተደረገው ስልክ ደግሞ አንድ መልእክት አለ " የአህላም ወንድም ነኝ ቴክስቱን እንዳየህ ደውልልኝ ለአስቸኳይ ጉዳይ እፈልግሃለው" ይላል ፤ ግን አንድ ነገር ረበሽኝ የዚህን ያህል ሰዓት አህላም ስልክም አልደወለችም ቴክስትም አላኖረችም አህላም የት ሄደች?  አጐቴስ ለምን ደወለ? ወንድሟስ የዚን ያህል ለጥብቅ ጉዳይ ለምን ፈለገኝ ?

ክፍል አስራ አራት ይቀጥላል………

@fonkabcha1
@fonkabcha1
287 viewsPassenger, 19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 22:29:57 ​​እሱም እናቱ ለተስማማችበት ነገር ፍቃደኛ መሆኑን ተናግሮ ግን አንተን ማየት እንዳለበት ጠይቆ ዛሬ አንተ ባታውቅም ሱቅ መጥቶ አይቶህ ነው የሄደው ፤ ምላሹንም ለአጐትህ አሳውቆታል ከአጐትህ ጋር በዝርዝር እንዳወሩ እና በተግባቡት መሰረት የዛሬ ሳምንት ሽማግሌ እንዲላክ ቀን ተቆርጧል …… አህላምዬ አሁን ደንገጥ አለች ፈገግታ የተቀላቀልበት ዕንባዋን አፍስሳ ማሚን አቀፈቻት የእስካሁኑን ሰምታ የሽማግሌውን ቀን መቆረጡን ግን አላወቅችም ነበር… አዎ ወንድ ነኝ ዛሬ ግን ተሸነፍኩኝ ዕንባዬ ቀድሞኝ ወረደ አዎ ዕንባ " 99% ስሜት ሲሆን 1% ነው ውሃ" ስሜቴ ገንፍሎ ወጣ ማሚን አቅፍኳት ሕይወቴን አቀለለችልኝ ፣ የመከራውን ክምር የናደቸው መስሎ ታየኝ አህላምና እኔ ልንጋባ ሰርግ ብቻ ቀረ… ሽልማቴን አገኝሁኝ ምኞቴን በእጄ አስገባሁኝ ፤ የመጀመርያ ልጇን የምትድረው ማሚ ደስታዋ ወደር አጣ የደስታ ስካር እና ዕንባ ተፈራረቀባት ፤ ሶስታችንም ያለአንዳች አስካሪ መጠጥ በደስታ ብቻ ሰከርን ……… የካቲት 3 / 2004 ዓ/ል ሽማግሌ ተላከ እኔም የቤት ዕቃዎችን ከአህላምዬ ጋር ሟሟላት ጀመርን ፤ የሽምግልና ሂደቱ ብዙም አድካሚ አልነበርም በሁለታችንም ቤተሰብ መሀል ሽማግሌ ሁነው የተገኙት የሚተዋወቁ እና በብዙ ማህበራዊ ጉዳይ የሚገናኙ ሰዎች እንዲሁም ባባን የሚያውቁት ሰዎች ነበሩ የሰርግ ቀጠሮ ተያዘ…………...


ክፍል አስራ ሶስት ይቀጥላል


@fonkabcha1
@fonkabcha1
219 viewsPassenger, 19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 22:29:57 ​​​​​​​​​


"ሴት አላምንም"

ክፍል 12

ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ

……… የራስምታቱ መንስዔ የድካም ስሜት እና ፀሐዩ እንደሆነ ስለገባኝ ፊቴን ታጥቤ ወደ መኝታዬ አመራሁኝ…ምሽቱ በንጋት ተተካ ህይወትም እንዲህ ናት የጨለመበት ጊዜውን ጠብቆ ወገግ ይልለታል ፣ ሳቁን ያጣ በቀኑ ይስቃል አየህ ለዚህ ነው አንተ አይደለህም የምትስቀው ጊዜህ ነው የሚስቀው የሚባለው…… ብቻ ነግቷል የዛሬው ማለዳ ይለያል ከአህላምዬ ጋር የፍቅራችን ጥንስስ የጀመርንበት ነው…… ማታ አህላምዬ ቴክስት ልካ ነበር " ባየሁህ ጊዜ የእኔ እንደሆንክ አንድ ነገር ነግሮኛል ልቤ ስለአንተ ጠየቀኝ እናም ቀስ በቀስ ልቤን ሞላህው ከጅዬህ ነበር በመጨረሻ አገኘሁህ አፈቅርሃለው" …… ልዩ የሆነ የፍቅርና የደስታ ስሜት ተሰማኝ እኔም… የዓለም ሴቶች ሁሉ እፊቴ እንደ ዝናብ ጠብ ጠብ እያሉ ቢመጡ አይኔ ባንቺ እንጂ በማንም አትሞላም የአይኔ ማረፊያ አፈቅርሻለው" ብዬ ከአልጋዬ ተነሳሁኝ ማሚ ቀድማኝ ተነስታ ስለ ነበር ሳሎን ስገባ ቁርስ ተዘጋጅቶ የእኔን መምጣት ነበር የሚጠበቀው……ከማሚ ጋር እየበላን በመሀል ስለእኔና አህላም ሁልንም ነገርኳት በህይወት ዘመኔ ያንን ፈገግታና ደስታዋን አይቼ አላውቅም … በሰሚራ ጉዳይ የነበረውን ጥርጣሬ በፊቷ ምላሽ ተወገደልኝ…… ያንን ከውብ አንደበቶቿ የሚወጣውን ምክሯን ማዥጐድጐድ ጀመረች።

የኔ ልጅ! ከአባትህ ሞት በሗላ አንድ ቀረኝ የምለው አንተ እና የአንተን ስኬት ነበር ፤ በአባትህ የቀረኝን ፍቅር በአንተ እሞላዋለው ብዬ አስብ ነበር ፤ አግብተህ እና ወልደህ ማየት ከምንም በላይ ለእኔ ስኬት እና እርካታ ነው። ተማሪ ነህ ብዬ ስለማስብ የማግቢያህ ጊዜ ይርቅብኛል… ግን በቂ ሃብትና ንብረት አለህ ባል ለመሆን እድሜ ሳይሆን አስተሳሰብ በላጭ ነው ፤ እድሜያቸው አርባ ሁነው ግን ጭንቅላታቸው የ 10 ዓመት እንዳለ ሁሉ ፣ እድሜው 20 ሁኖ አስተሳሰቡም የበሰለም አለ። ልጄ ማስጨነቅ እንዳይሆንብኝ ብዬ እንጂ ከሰሚራ ጋር ብታጋቡልኝ ብዬ አስብ ነበር ዛሬ ግን የራስህን ሰው አምጥተሃል ፤ ምርጫህን ልጋፋህ የምፈልግ ሰው አይደለሁም የመረጥካትን ልጅ ባላውቅም አንተን ልጄን ግን አውቅሀለው… ለልጆችህ እናት የምትሆንዋን እንደመረጥክ አምናለው… ልጄ ውበት እና መልክ አስፈላጊ ነው ግን የትዳር መሰረቱ እርሱ አይደለም እስኪ ልጠይቅህ? ለምንድን ነው ያፈቀርካት? የማሚ ጥያቄ ነበር መልካም እና ውብ ሴት ስለሆነች ፍቅርን ሰጥታ መቀበል የምትችል ንፁህ ሴት ስለሆነች ነው ማሚ……… ዕይታህ መልካም እና ጥሩ ነው ፤ ስለ ፍቅር ስታወራኝ ስለትዳር የነገርኩህ ለሁሉም ጥያቄዎች ብዙ ምላሾች ሊኖራቸው ይችላል ፤ ነገር ግን የመዋደድ እና የፍቅር ምላሹ ደግሞ ኒካህ ብቻ ነው። አንተም እርሷም ተማሪ ናችሁ ታድያ የእናንተ ልብ ፈቀደ እንጂ የቤተሰቦቻችሁ ፍቃድ ገና አልተወሰነም… ልጄ አትደንግጥ እኔ በአንተ ሙሉ እምነት አለኝ የምትሆንህን መርጠህ ካመጣህ እቀበልሃለው ሁሉም ቤተሰብ ግን እንደኛ ላይሆን ይችላል… የሁልም ልጅ ለቤተሰቡ ውድ እና እንቁ ነው ስለዚህ የቤተሰቧን ምላሽ አጣራ… ፈገግ ብላ ለአንተ ሌላ ሽማግሌ አያስፈልገውም እኔ ሽማግሌ እሆንልሃለው አለችኝ…… ቀጠል አድርጋ ልጄ? በቂ ሀብትና ንብረት አለን ከዚህ በሗላ ሱቁም መኪናው የአንተ ናቸው ፤ ደስተኛ ሁነህ እንድትኖርልኝ እፈልጋለው ከቻልክ ልጅቷን አምጥተህ አስተዋውቀኝ አለችኝ…… ልቤ በደሰታ ጮቤ ረገጠ ሁሉም እናቶች እንደ እኔ እናት ቢሆኑ ብዬ ተመኝሁኝ ግና የእናት መጥፎ የለውም… … የእኔና የአህላም ፍቅር የዘመናት ውጥን ሳይሆን የቀናቶች ድምር ውጤት ነበር ፤ ከእርሷ ጋር ባሰለፍነው ጊዜ የተገነዘብኩት ከእርሷ ውጭ መኖር እንዳማልችል ነው፡፡

የ 12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና አለቀ ፣ ክረምቱም በነፃነት እና በፍቅር አሳለፍን ውብ ክረምት ፤ ክረምት አሁን ነው የጀመረው ወይስ ድሮም ነበር። ድሮም ከነበረ የአሁኑ ይለያል ካልነበረ ግን ክረምት ማለት እኔና አህላምነን ማለት ነው…… ማሚን ከአህላም ጋር አስተዋውቅያት እኔን ባይተወር አድርጋኛለች ፤ የየትኛውም እናት እንደ ባህላችን ከጋብቻ በፊት ከልጁ ሚስት ጋር የዚህን ያህል ቅርርብ እንዲኖር አትሻም ፤ የእኔ ማሚ ግን የሴት ልጅ ምኞት አልያም ደግሞ በልጇ ሚስት የመሸነፍ ጉጉት ባላውቅም ወሬያቸው ልዩ ሁኖዋል ሲያሻቸው እኔን ባዳ አድርገው ይጫወታሉ…… …እኔም ስራ ውዬ መግባት ከጀመርኩኝ ሰነባብቻለው ፤ አህላምም የኮሌጅ ትምህርቷን ቀጥላለች ፤ ማሚም የስራ ድርሻዋን እኔ ስለተረከብኩት አህላም እረፍት ስትሆን ገበያ እየወጡ ይመለሳሉ………… ምን ዓይነት ድንቅ እና ውብ እናት ነች ፤ እኔ እና አህላም እንደ ቀልድ ሁለት ዓመት ሞላን ማሚና አህላም ግን ግንኙታቸው የወራቶች ሳይሆን የዘመናት ነበር የሚመስለው… … ነፍሴ ሀሴት አደረገች በምድር ላይ ሁለት ውብ እና ውድ ነገሮች አሉኝ እናቴ እና አህላምዬ …… ዛሬ አዲስ ቀን ነው ማማ ሁለታችንንም በአንድ ጉዳይ ልታናግረን እንደምትፈልግና ሱቅ ቶሎ ዘግቼ እንድመጣ ጥብቅ ማሳሰብያ ሰጥታኛለች …… የማሚን ቃል አክብሬ በጊዜ መጥቻለው ማሚና አህላም አብረው ቁጭ ብለው እየተጫወቱ ነው…… ዛሬ ቁም ነገር የያዙ ይመስላል… ሰላም ብያቸው ልብስ ልቀይር ክፍሌ ስገባ የሚያምር አበባ እና ወረቀት ተቀምጦልኟል……" ከመተነፍስ እና አንተን ከመውደድ መካከል ለመምረጥ ብገደድ ሁቢ .... የመጨረሻውን እስትንፋሴን ተጠቅሜ አንተን መውደዴን እገልፅልሀለው" አፈቅርሃለው የወደፊት ባሌ ከሚስትህ አህላም የሚል ነበር። ፈገግ አልኩኝ እናቴ ሁሌም ቢሆን ዱዓዋ ወግ የሚገባት ሚስት ይስጠህ ነበር… ወግም ፍቅርም የሚገባትን ልጅ አድሎኛል…… የጓደኛዬ ወግ ትዝ ብሎኝ ሳቄን ለቀቅኩት ሰዒድ " እንደምንም ብለህ ፍቅር የምታውቅ እና የከተማ ልጅ አግባ ፤ የገጠር ልጅ አግብተህ ማታ ስትመጣ በር ላይ ጋቢ ለብሳ ነው የምትጠብቅህ ሲያሻትም ያንን ሁለት ዓይነት ካልሲ ለብሳ ፣ "romantic" ነገር አታውቅም ስለዚህ ተጣጥረህም ቢሆን የከተማ ልጅ አግባ አንተን ባታከብርህ የተጋባቹበትን ቀን ታከብርልሃለች ይልና ድክም ብሎ ይስቃል ፤ ሳቁ ታወሰኝ እና እንደሱ ፈገግ አልኩኝ……… ሳሎን ገብቼ እነ ማሚ ጋር ተቀላቅዬ አንድ ሁለት ጨዋታዎች ጣል አድርጌ ለማሚ መድረኩን ለቀቅኩላት…… ማሚ አንቺ እና ልጅሽ አህላም እኔን እንደ ጐረቤት ልጅ አድርጋችሁኝ ምን አድርግ ብላችሁ ነው የጠራችሁኝ "ኪራይ" በወቅቱ አልከፈልኩም ብዬ ፈገግ አልኩኝ በውስጤ ለአህላምዬ ለዛሬ ስጦታዋ ምላሽ ምን መስጠት እንዳለብኝ እያሰላሰልኩ ነበር…… ማሚም ቁጭ በል እስኪ ብላ …… ዛሬ የፈለግኳቹ የሁለታቹንም ግንኙነት ወደ ትዳር የመቀየር ሃሳብን ይዤ ነው…… ሰዒዲዬ አህላምን በደንብ አውርቻታለው በጨዋታ ጨዋታም የእርሷ ቤተሰብ ከአጐትህ ጋር ቅርርብ አላቸው… አንተ ሳታውቅ አህላም ለእናቷ እንድትነግራት እና ሃሳቧን እንድታሳውቀኝ በነገርኳት መሰረት…… መልካምን ምላሽ ይዛ መጥታለች …… አጐትህም አውቆ ደስ ብሎታል አሁን የቀረው ወንድሟ ነበር ለወንድሟ ደግሞ አህላምና እናቷ እንዲነግሩት ተነጋግረን ነበር… በእናቷ ሃሳብ አጐትህ እንዲጨመር አድርጌ ትላንት ማታ አናግረውት ነበር።
253 viewsPassenger, 19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 20:38:54 ​​​​​​​​​​​



ሴትን አላምንም

ክፍል 11

ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ



ውበቷ ገደብ ጥሶ ተሸነፍኩኝ……የውቦች ተወካይ መሆኗ ፍንትው ብሎ ተገለጠልኝ ፤ የቆንጀዎች መሪ ደረቴ ላይ መኖሯ አቅም አሳጣኝ… ጥቂት የማይባሉ ፀጥታ የሰፈነባቸው ሰከንዶች ውቢቷ ደረቴ ላይ ተለጥፋ አለፉ ፡፡

ነፍሴ እንደ ጠዋት ፀሀይ እንደ ጠዋት ወገግታ አህላምዬን ናፍቋል ፣ ድንቅ ገጣሚያን ፣ ውብ ሙዚቀኞች ፣ ታዋቂ ጋዜጠኞች ፣ ከያኒያን ፣ ሰዓሊያን በዙሪያችን ስለእኛ ለመዘገብ የቆሙ መስሎ ታየኝ። …… ሁለታችንም በፍቅር ዓለም ውስጥ ሰጥመናል ፤ የሰውነታችን ሙቀት ከትክክለኛው የሰው ልጅ የሙቀት መጠን ያለፈ መሰለኝ። ድንቅ የመፈላለግ ስሜት…… አጠገቤ ያለችው ፀሀይ ወይስ ጨረቃ የማልጠራጠረው ከሁለት አንዱ አጠገቤ እንዳለ ነው……እምቡጥ ፅጌረዳ የመሰለው ከንፈሯ ውብነቱን ሳይለቅ እየተንቀጠቀጠ ተከፈተ ፤ አይኗን ጨፈን አድርጋ ከአንገቷ ቀና ብላ ወደእኔ ጠጋ አለች ሳናዛቸው ከንፈሮቻችን ተጋጠሙ… አንዱ እጄ  አንገቷን ሌላኛው እጄ ወገቧን ይዞ በፍቅር ዓለም ውስጥ ሰከርን ከልካይ የሌለበት ምሽት ይሄን ውብ ሰዓት ማንስ መጥቶ ይከለክለዋል ፣ የትኛውስ ማዕቀብ ያስቆመዋል፣ የከንፈሬን ማህተም ከንፈሯ ላይ አኖርኩኝ አዲስ ህይወት ሁለታችንም ወደ ማናውቀው ዓለም…  የፍቅር ዘማሪዎች ከያሉበት ወጥተው ውብ ዝማሬያቸውን አዜሙልን … … የዘላለም ይሁን ብለው መልካም ምኞታቸውን ተመኙልን ፣ ትንፏሻ ፍጥነት አለው የፍራቻ ትንፋሽ የማይሰማ የድንጋጤ ጩኸት ግን ደግሞ ደስታ የምን ሀዘን ማን ነው የሞተው የምትል ትመስላለች…… እውነትስ ማን ነው የሞተው?

እነዛ ትናንሽ ከዋክብቶች ስለእኛ ውብ እና ደማቅ ብርሀናቸውን ወደ ምድር ላይ አወረዱት …የማትጠገብ ሴትና የምድራችኝ ብቸኛዋ ባለ ውብ ከንፈር ፣ የክፍለ ዘመናችን ልዩ ሴት ከንፈሬ ላይ የዘላለም አሻራዋን  አኖረች ፤ ልለቃት አልፈለግኩም እሷም መሄድን አትሻም…የምናየው ነገር ሁሉ የሚያምር የምንሰማው ነገር ሁሉ ጥዑም ዜማ የተላበሰ መሰለ።

ከብዙ መሳሳም  ቡሀላ ተላቀቅን ህልሜ ዕውን ሆነ ለትንፋሽ ሳይሆን ለፍቅር ስሜት ከንፈሬን ከከንፈሯ ጋር አላተምኩኝ… … የመኖር ጉጉቴ ጨምረ የእርሷም እንዲሁ ፤ ወደ ጆሮዋ ጠጋ ብዬ "አፈቅርሻለው" የማለዳ ሀሣቤ አንቺ ነሽ ብዬ አንሾኳሸኩ.. ምንም ማሰብ በማይኖርብኝ ግዜ እንኳን አስብሻለሁ...አንቺን ማፍቀር መከተል የህይወቴ አንዱ ምሣሌ አድርጌዋለሁ አፈቅርሻለሁ..ደጋግሜም አፈቅርሻለው..ባንቺ ማፍቀር ውስጥ ቀኔን ጀመርኩ ምሽቴን ውብ አደረግኩኝ  ....ሽልማቴ ነሽ የእኔ ፍቅር ብዬ ዓይኗን ተመለከትኩኝ  በፍቅር ዕንባ የተሞሉ ዓይኖቿ ውስጥ አንዳች የፍቅር ደሴት ይታየኛል…  ወደ ጆሮዬ ተጠግታ በሹክሹክታ "አፈቅርሃለው" ብላ ከንፈሬ ስማ ሳታየኝ ዞራ በፍጥነት ሄደች… በዚች ቀን የፍቅራችን መሰረት ተጣለ፣ የዛኑ ቀን ግንባታው ተጀመረ በጠንካራ የመፈላለግ መሰረት። 

ሄደች የሰላም እርግብ ከአጠገቤ ርቃለች ፤ ከደቂቃዎች በፊት ሁሉ ነገር እጄ ላይ ነበር ውበት፣ስብዕና፣ፍቅር አሁን ግን ሄዳለች… ህልም ወይስ አሁናዊ ሁኔታ?   በፍጥነት መኪናዬን አስነስቼ ጉዞ ወደ ቤት ………  ዛሬ የፍጥረት ውሃ ልክ የእኔ ሁናለች… ጭር ያለ ምሽት  ጭር ያለ መንገድ ላይ በፍጥነት እየነዳሁኝ ነው። ቀስ ብዬ የምነዳው ማሚ አጠገቤ ስትሆን ብቻ ነው መኪና  ስነዳ ያየኝ ሰው እና በህይወት እንቅስቃሴ የሚያቀኝ ሰው ሁለት ገፀ ባህሪያቶችን ይዤ የምጫወት ነው የሚመስለው። "ምን አልባት የአህላምዬን ፎቶ  30 ላይ አድርጌ" 30 የሆነው በምክንያት ነው ካላልኩኝ በስተቀር ይህን ባህሪዬን መቀየር አልቻልኩም … ……

ቃል ገባው በሰው ፊት
ይኸው በአደባባይ
ከአንቺ ሌላ ላላይ
የሱ ፍቃድ ሆኖ
አንቺን አግኝቻለው
ምን እፈልጋለው……

ይህ ውብ ሙዚቃ የዘፈን ምርጫ በሚሰኘው የሬዲዬ ፕሮግራም ላይ የተጋበዘው ዘፈን ነበር።እኔም ቃል ገብቻለው በአደባባይ ብቻ አይደለም በጨረቃ ፊት እስከመጨረሻው እስትፋንሴ ድረስ ከአህላምዬ ላልለይ ………… ቀን ማማን አላየሗትም ናፍቃኛለች ፤ ስለ ህይወት ስታወራና ስትመክረኝ ነገሮችን ቀላል ታደረግልኛለች… በ ባባ መሞት ልቤ ተጐድቶ ተስፋ በቆረጥኩበት ሰዓት የእድሜ ልክ ምክር የሚመስለው ንግግሯን እንዲ በማለት ነበር የነገረችኝ……… ሰዒደዬ እባክህ አትዘን !ሀዘን እኮ "ንፁህ ውሃ ስታይ መርዝ ፣ ፅጌሬዳ አበባ ስትመለከት ቁልቋል ፣ ማራኪ የአትክልት ቦታ ስታይ የተቃጠለ ምድረ በዳ ፣ በሰፊ ምድር ላይ ጠባብ እስር ቤት እንድታስብ ያደርግሀል።

በአደጋ የተነሳ ስታዝን ሌላ አደጋ ፣ በድህነትህ ምክንያት ስታዝን ድህነትን ትጨምራለህ ፣ ሀዘንህን ትተህ መልካምን ነገር አድርግ ለባባ የሚጠመቀውን አድርግለት አባትህ መልካም ሰው ነበር ስለ መስጠት ሰብኮ እና ሰጥቶ ነው ያለፈው ። ………ውዷ ባለቤቴ አንቺ የምትሰጪያት ጠብታ ከልብሽ ከሆነ በእጥፍ ይሰጥሻል። በምትሰፍሪው መስፈርያ ይሰፈረልሻል በሰጠሽው ልክ ይሰጥሻል ስለዚህ "አመድ አፋሽ ሆንኩ" ከማለትሽ በፊት አመድ ሰተሽ ከሆነስ? መስጠትን ብቻ ሳይሆን አሰጣጥሽ ወሳኝነት አለው አንድ አንዴ ከመንጠቅ የማይተናነስ መስጠትም አለ ይልና ግንባሬን ይስመኛል።

የኔ ባል? እለዋለው

ወዬ የአይኔ ማረፍያ የዘውትር መልሱ ነበር።

ንግግሮችህ ሁሉ ይማርኩኛል ስለው "መፅሀፉን ስለምትፈሪው እኮ ነው ግለጪው ያልኩሽን ሁሉ እርሱ ላይ ታገኚዋለሽ ይለኝና ይስቃል" እኔም አኩራፊዋ እናትህ ያኮረፍኩኝ መስዬ ወደ መኝታ ክፍል እገባለው እሱም ተከትሎኝ ይመጣል።

ሳታስበው እንባዋ ይቀድማታል ስለሱ ስታወራ… … ትዝታዬን እየቃየኝሁ መኪና ከፊት መኖሩንም እንኳን አላየሁም ነበር መኪናው አልፎኝ ስሄድ ነው የባንንኩት "አልሃምዱሊላህ" ተረፍኩኝ ዛሬ ለማሚ ሁሉንም ነገር መንገር አለብኝ ስለ አህላምዬ "እንደምትወዳት" ተስፋ አደርጋለው ማሚ ደስታዬ ደስታዋ ነው።  የመኪናውን በር አልፌ እንደገባሁኝ ማሚ ከሁለት ሴቶች ጋር ቁማለች ማምሸቴ ገባኝ ቢሆንም ስለ አህላምዬ ስነግራት እንደምትረጋጋ አሰብኩኝ…  "ሰሚራ" አልኩኝ ድንገት ልቤ እየደነገጠ ማሚ ስለዚች ልጅ ሁሌ ታወራኛለች ከቤታችን ሁለት ግቢ ቀጥሎ ነው መኖርያቸው።

እናቷ የማሚ ጓደኛ ነች ልጇም እርሷም ጥሩ ሰዎች ናቸው። ለእርሷ ነው ምድርህ ብላ አንድ ቀን ማሚ የቀለደችው ቀልድ ትዝ አለኝ እና ደነገጥኩኝ ፤ በህይወቴ የመጣች ስንክሳር መስላ ታየችኝ በማታውቀው ነገር እየሰደብኳት እንደሆነ ቢገባኝም  ግን  በዚህ ሰዓት ከአህላምዬ ውጪ ማንንም ማየትም ስለ ማንም ማሰብ አልፈልግም……ማሚ ና እንጂ ሰው ሰላም በል "ሰሚራ" ጐረቤት ሁናቹ እስካሁን እንዴት አትግባቡም ፤ ይሄኔ የሌላ ሰፈር ወንድ ልጅ ስልክ ከስልክሽ እኮ አየጠፋም አለች እናቷ… የሰሚራ እናት አራዳ ነች የእኔ ማሚ ደግሞ "የአራዳዎች አለቃ" ሰላምታ ተለዋውጥን ወደ ቤት ገባሁኝ ድንገት ራስ ምታት ጀመረኝ ጐንበስ ስል ከአፍንጫዬ ደም እየፈሰሰ ነው ኻዲማችን ደሜን ስታይ ጩኻ ስለ ነበር እነ ማሚም እየሮጡ መጡ።

ክፍል አስራ ሁለት ይቀጥላል ...

@fonkabcha1
@fonkabcha1
303 viewsPassenger, 17:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 20:37:41 ​​​​​​​​​


ሴትን አላምንም

ክፍል 10

ፀሀፊ ሱለይማን መሀመድ


መኪናውን ወደዳር አቁሜ ስመለከት ቴክስቱ የአህላምዬ ነው። ተጣድፌ ከፈትኩት

ሰኢዲዬ?
 … የሳቅ ረሀብተኛ ዘወትር አልቃሽ ሴት ሁኜ ነበር የተገናኝነው ፤ ያሳለፍኩት ህይወት ጨላልሞብኝ የህይወት ለዛው ጠፍቶብኝ ስባክን እና ስብከነከን ቆሜ እንዳልራመድ አቅም ያጣው ሆኜ ሳለው ነው መጥተህ የህይወትን ቀጣይ አቅጣጫ ያሳየህኝ እህቴ ለኔ ከምንም በላይ ነበረች። ከእርሷ ውጪ ህይወት ሞት መስሎ በሚታየኝ ሰአት ድንገት የህይወትን ብርሃን አብርተህ አሳየኝህኝ "ሁሉም ሰልፈኛ ነው ተራውን ጠባቂ "ያልከኝ ምክር እህቴን አስታወሰኝ አህላምዬ "ሰው ታመመ ብለሽ ብዙ አትጨነቂ ሁሉም ሰው ዛሬ ባይታመም ነገ ፣ ዛሬ ባይሞት ነገ ይሞታል የተራ ጉዳይ ነው ስለዚህ ለሚመጣው የህይወት ፈተና እራስሽን አዘጋጂ" ትለኝ ነበር።

 እርሷም ተራዋን ጠብቃ ሄደች ፤ ግን አንተን ተክታልኝ የሄደች መስሎ እንዲሰማኝ አደረግከኝ። እውነት በጠፋበት ዘመን የእውነት ሰው ሆነህ አሳይተህኛል ፤ በእጆችህ የነካሃቸው እግሮቼ ፣ ከጉድጓድ ውስጥ በእቅፍህ ያወጣህበት የትህትና ጥግ ፣ ወንድሜን ተክተህ  ከቤት ወደ ት/ቤት ያመላለስክበት ስብእናህ ከልቤ የሚጠፋ አይደለም ፤ ዛሬ ደግሞ ከመራራው ሀዘን መለስ ብዬ እንዳስብ ረድተህኛል ለዚህም ከልቤ አመሰግናለው ከትምህርት ቤት የቀርሁባት ያቺ ቀን እህቴ በጠና ታማ ስለ ነበር ነው።

ነግቶ እስከማይህ ናፍቆቴ ብዙ ነበር ጥላዬ መስለህ ትታየኛለህ አደራ ከጐኔ ሁነህ አበርታኝ………። ከአህላም የተላከው መልእክት ነበር

 " እውነተኛ ሳቅ እና ደስታ ውስጤ ሲፀርስ ተሰማኝ…  እሷን የእኔ አድርጌ አሰብኳት መላ አካለቴ ጆሮ ሆኖ ስለእርሷ ማዳመጥ ፈለገ ፣ ሁለመናዬ የእርምጃዎቿን ኮቴ ማዳመጥ ጀመሩ።

ተስፋ ጭንቅት እንዲሁም ፍቅር አንድ ላይ ተዋህደው ነፍሴን በፍቅር ውቅያኖስ ውስጥ ሲከቷት ታየኝ… አህላምን ሊወስዳት የመጣው ችግር  ሲወረፍ ታየኝ… … ምን ያህል በፍቅሯ እውር እንደሆንኩኝ ባየች ብዬ አስብ ነበር ፤ ዛሬ ግን የፍቅርን ጭላጭ ሳትጐነጨ አልቀረችም ቴክስቷ ለኔ ከምንም በላይ ዋጋ ነበረው… … የአንድ አንድ ሰው ኖሮም ሞቶም ጠቃሚነቱ ጉልህ ነው።

የአህላምዬ እህት ሞታ የሚወዋዳዱ ሰዎችን ህይወት ግን አስቀጠለች ፤  ህልሜን በእውኑ አለም ውስጥ ያገኝሗት መስሎ ታየኝ።  ማለዳ የወፎችን ድምፅ በእቅፌ ውስጥ ገብታ ስታዳምጥ…  በፍቅር ስንወዳደስ ፣ በፍቅር ስንጐራረስ ፣ በአንድ የህይወት ጣራ ውስጥ ህይወትን አብረን ስንቃኝ ታየኝ እና ፈገግ አልኩኝ።

ስልኬን አውጥቼ መልእክቴን አኖርኩላት……

አህላምዬ ከልብ አመሰግናለው እውነታው ይህ ነው………​ልቤ በአንቺነትሽ ሀሴት ተሞልታለች አንቺ በህይወቴ ምዕራፍ ከመጣሽ ጊዜ ጀምሮ አዲስ ተስፋ እና አዲስ ሃይል አግኝቻለው … አይኖቼም በድካም አይፈዙም ራስ ምታትም ሆነ ነስር ከዛች ልዩ ቀን በሗላ ተመልሶ አያውቅም ሀኪሜ ሁነሽ አዳንሽኝ ፈዋሼ ሁነሽ የመኖር ህልሜን በእጥፍ ጨመርሽው።

አህላምዬ?

ልቤ ዘወትር ስላንቺ ያስባል ፣ አይኖቼ አንቺን ብቻ ለማየት ያማትራሉ ፣ ጉልበቶቼ ወደ አንቺ
ለመጓዝ ይበረታሉ ፣ በልቤ ዙፋን ነግሰሽ ተሞሽረሻል  ………… ። መልእክቴ ተቋጨ "አፈቅርሻለው" ብዬ ላፍረጥርጠው? አዎ አፍቅርያታለው እሷን ወደ ህይወቴ ካመጣሁኝ ቡሗላ አይበርደኝም ፣ አይጠማኝም ከምግብ የበለጠ የሚያጠግበኝ፣ ከመጠጥም ይልቅ የሚያረካኝ፣ ፍቅሯ በውስጤ አለ። "እነዚህ ቃላቶች ሁሉ የኔ ቢሆኑም ፍቅሬን አይገልፁልኝም " ግን አሁን አፈቅርሻለው አልላትም"። ለሁሉም ጊዜ አለው።


የመኪናዬ በር ተንኳኳ …… አንዲት ላይዋ ደምቆ ውስጣ ግን አንዳች የመሸነፍ ስሜት የተላበሰች ሴት ነበረች "ሴተኛ አዳሪ"። "ማልወደው ቃል"

መስኮቱን ዝቅ ሳረገው ሳልናገር ፈጥና ወንድሜ ቦታውን ልቀቀው እንጂ የስራ ቦታ ነው ከፈለግክ አንዳችንን ይዘህን ሂድ ካልሆነ ተንቀሳቀስ አለች ቆጣ ብላ።

እሺ ብዬ መኪናዬን አስነስቼ ሄድኩኝ አሳዘነችኝ ግን ደግሞ ምን ታድርገው ። የረከሱ ወንዶች የገንዘባቸው መለኪያ የስሜታቸው ማርኪያ አድርገዋቸዋል ሴትን ልጅ እንዴት ለርካሽ ነገር ይጠቀሟታል?

 ሴትን ልጅ "ከእንብርቷ በታች ላለው አካሏ ሳይሆን ከአንገቷ በላይ ስላለው ጭንቅላቷ ብሎ የሚቀርብ ወንድ ከተማው ላይ የለም እንዴ"? የሴትነትን ዋጋ ያላወቁ ወንዶች ከስሜታቸው ቀድሞ ለህሊናቸው ቢያስቡ ምን አለ? አንዲትን ሴት ወደ መልካም ህይወት መምራት ከመከራ ህይወት ማውጣት የህሊና እረፍት እንጂ ሌላ ምንን ይሰጣል ?

እነዚህ ስጋ ነጋዴዎች! ሴትን አረከሷት አልኩኝ አንድ የግጥም ስንኝ ትዝ እያለኝ

የሌሊት ስጋ ቤት
ይሄ ስጋ መሸጥ ያተርፋል እያሉ
 ያዋጣል እያሉ
የቀን ሳያንሳቸው
እራፊ አሻርጠው ማታም ይወጣሉ
ስጋ እየተስማማው ስጋ እያጣፈጡ በላተኛው ሁሉ
ቀን የበሬ ገዝተው
 ባዋዜ አዋህደው ፤
 ሲቆርጡ እየዋሉ
 ሲጠብሱ እየዋሉ
ማታም እየጠጡ
 ነፍሳቸውን ስተው
 የሰው ስጋ ገዝተው
ዝሙት ይሰራሉ ፤
የበሬን ጥብስ ጥጋብ
 ፀሀይ እንደገባች በሰው ያበርዳሉ፡፡ አልኩኝ ።

በተደጋጋሚ እነ አህላምዬ ጋር በለቅሶው ሰበብ መሄድ አብዝቻለው ፤ አንዳች የመቀራረብ ስሜት ሁለታችንም ላይ ይታያል…… መመላለሴን ያዩና ስወጣ ከአህላምዬ ጋር የሚመለከቱኝ እየታዘቡኝ መስሎ ታየኝ "በፍቅሯ ሽባ ልፍልፍልስና ጠውላጋ ነው ብለው ያሙኝ እየመሰለኝ ፈራ ተባውን ተያይዤዋለው።

ይበሉዋ ደግሞ ምን ገዶኝ ልክ አይደሉ እንዴ ? በማላዘው አይኔ እየናፈቀችኝ ፣ በከደንኩት አይኔ ደግሞ እያየሗት አይደል? ቃል ባጣው ምላሴ አልሰብኳትም ፣ በድን አካለቴ እሷን አላለም ? የእርሷ ምርኮኛ ነው ቢሉ ምን ተሳሳቱ? ………… ዛሬ ከሌላው ጊዜ የበለጠ አምሽቻለው አህላምዬ መኪና ድረስ ልሸኝህ ብላ  አብራኝ ወጥታለች… ፈገግታዋ እየተመለሰ ፍንድቅድቅ ሁና እያተየችኝ ነው "አልሃምዱሊላህ" የሁለት ሰው ደስታ ተመለሰ የእኔም ፣ የእርሷም "በኔ ውስጥ እሷ አለቻ"………… አስፓልቱ ዳር ቆመን  ስለ ቤተሰብ እያወራን እርሷም መበርታት እንዳለባት እያወራን  አንድ መኪና ከላይ  እየተመዝገዘገ መጣ…………እጇን ስቤ ወደ ደረቴ አስጠጓሇት መኪናው አለፈ ፤ እኔና እሷ............

ክፍል አስራ አንድ ይቀጥላል……

@fonkabcha1
@fonkabcha1
284 viewsPassenger, 17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ