#ምርጥ ( #ምርትነሽ_የማነ) እቴትዬና..... እሜ አደዬና ......ሀርሜ በየ ፈርጀ ........ፈርጁ በእያንዳንዱ ቋንቋ ፥ ቃላት ቢወዳጁ አንቺን .....እኮ እናቴ የጠዋት አስኳላ ፥ የልጅነት ሀብቴ ኑር አንተ ለኔ .......ባይ ቅንጣት ሳይታወስ ፥ ላንቺ ያንቺው ጉዳይ በጉያሽ አቅፈሺኝ ፥ በጪንጫ ተኝተሽ ውሀ ባፍሽ ርቆ ፥ ወተቱን ያጠጣሽ ማጀት ያጠቆረሽ ረሀብ ያከሳሽ ጎኔን ....... ጨርቄን...... ማቄን የሚሉት ጥበቃ ፥ ከራስ በላይ ንፋስ ፥ ሰይሞ መዳከር ላንዲት ነብስ ስስት ላንድ አካል መንቧቸር ከራስ በላይ ልጄን በሚል ልግስና ፥ እድሜን በመቸርቸር ብ ርክ በማለት ፥ ብርክሽን የረሳሽ በመከነ ቀለም ፥ ብዕርሽ የጠፋች። ያ..............#ፀሀይ ውበትሽ ኩሽና ተሳስሮ ፥ ከምጅጃ ግርጌ፥ ዕድያው የቀረ ወዘናሽ ተሟጦ ፥ ገፅሽ የጠቆረ በመጨናበስ #ነው አካልሽ ለጋሱ ፥ አይነ ግቡ መልኬን ፥ ዛሬ የወቀረ ። የአፍላነት ግዜሽ ጥንቡሳሱን ጥሎ ፥ ያለ እድሜሽ ያረጀሽ ደ ስታን ልክ እንደ መርዝ ለልጅ በመኖር ውስጥ ፥ ዘመንሽ የቀማሽ በአለሙ መሀል ፥ ለአለም እንግዳ ትክሻሽ የሳሳ ፥ ቅስምሽ የተጎዳ የህይወት ቀንበር ተጫኝ ለፍሠሀ ባዳ !! ሀኪም እናታለም #ኮስማናዋ #እናቴ!!! የህይወት መቅድሜ የጉም ቀን መብራቴ ተስፋ አለምሽ ይጥና #በርቺልኝ በሞቴ እናትነትሽ ነው ፥ በዚህ ልፋጭ አለም ፥ የቀን ክራሞቴ። የሰማዩ ንጉስ የምድሩም ጌታ ከምንም አብልጦ ፥ እናቱን ይወዳል ትንሽም ሲራሩ እናቴ ያሉ እንደው ፥ ምዕንተ ማርያም ፀሎት ይማለዳል ውህብቶ ብዙ ነው ፥ ዳና በመከተል ፥ በገፍ ይሰደዳል እናቴ ለሚሉት እናት መሆን ያውቃል ስለዚህ .... ልጄን ብለሽ አንቺ ፥ ፊቱን እንደ ሰማሽ ያብቃኝ .... አንቺም ያብቃሽ.... ለልጅ የተሰዋ አድሮ የበረታ ፥ የህላዌ ጥዋ ብሩህ ጀምበር ገጥሞ በልጅ የፈዘዘ ፥ ዳግም በልጅ ቀልሞ እንጥፍጥፍ አለም ....በእድሜ ስልቻ ፥ ጠብቆ ተቀምቅሞ እያጠነጠነ...... የግዜ ሰሌዳ ፥ በመቁጠሪያ ሲታሽ አድማስ ተሻጋሪ ... #ቦግ!!! ብሎ ማታሽ ውድ ሸማሽ ሆኜ ፥ መቀነት ያውለኝ ለውበት ...ለድጋፍ ፥ መጠቅለል የቀናኝ ገንዘብ ....መቋጠሪያ ውጋት ......ማባረሪያ ላዱኛ ቀን ብርታት ለጭንቅ ቀን ፅናት አድርጎ .....እኔን ላንቺ ፥ ፈቅዶልኝ ፈጥሪ የእናቱን ቀን አውጪ ፥ በወዘናው ጣሪ ግብ ቀንቶት ፅናቴ ሹልክ ብለሽ ወጥተሽ ፥ ከኑሮ ግርግር ከእንጉርጉሮ አለም ፥ ጠማማ ውንግርግር ምርቃትሽ ደርሶኝ ....መነን ሁኚ እናቴ ባንቺ ውስጥ እንደኖርኩ ፥ በኔ ትኖሪ ዘንድ ፥ ይባረክ ጉልበቴ። #አብርሀም_ተክሉ ( #መርዕድ) @fonkabcha1 @fonkabcha1 120 viewsPassenger, 19:00