2022-07-10 20:57:15
. #መፅሐፍ #ቅዱስ #ሲነበብ #መጀመሪያ #አሜን #ነው #የሚባለው!
መፅሐፍ ቅዱስ ህያው: እስትንፈሰ መለኮት: የእግዚአብሔር ቃል በመሆኑ ልንታዘዘው የሚገባ ባለ ስልጣን መፅሐፍ ነው።
መፅሐፍ ቅዱስን አለመታዘዝ ማለት እግዚአብሔርን አለመታዘዝ ነው።ምክንያቱም በውስጡ ያሉ ቃላቶች ተራ የሰው ንግግር ሳይሆኑ የእግዚአብሔር ቃሎች ናቸው።በሰው ቋንቋ ቢፃፉም የመለኮት እስትንፋስ ስላላቸው እና የእግዚአብሔርን ሀሳብ በውስጣቸው ስለያዙ ተራ ቃላት አይዱሉም የእግዚአብሔር ቃል ናቸው ስለዚህም ስልጣን አላቸው።2ኛ ጢሞ 3:16
ታዲያ መፅሐፍ ቅዱስን ስናነብ በፍፁም መታዘዝ እና በፍፁም መገዛት ሊሆን ይገባል።
መፅሐፍ ቅዱስ ሲነበብ መጀመሪያ አሜን ነው የሚባለው!ይህ ማለት መፅሐፍ ቅዱስን መጀመሪያ ስናነብ ሙሉ በሙሉ የሚለዉን መቀበል ነው ያለብን።ቃሉን እንዲህ ነው እንዲያ ነው ከማለታችን በፊት ቃሉ የሚለውን እና ቃሉን ስልጣኑን አምነን መቀበል አለብን።
መፅሐፍ ቅዱስን ስናነብ በዋህነት ልናነብ እና የሚለውንም በዋህነት መቀበል አለብን።ብዙ ጊዜ ቃሉን ለገዛ ራሳችን ለመተርጎም እንፈልጋለን የሚናገረውንም እንዲመቸን አድርገን እንተረጉማለን።ይህ ደግሞ የመፅሐፍ ቅዱስን ስልጣን አለማክበር ነው! ስለዚህ ቃሉ የሚለንን በዋህነት መቀበል አለብን።መቀነስ ያለብንን: መጨመር ያለብንን: ማድረግ ያለብንን: ማድረግ የሌለብንን: ማወቅ ያለብንን: ማወቅ የሌብንን: በሙሉ ስልጣን ያስተምራል እኛም በሙሉ ስልጣን መቀበል አለብን!
ለዚህ የያዕቆብ መልዕክት ላይ ሲናገር:-
“........ነፍሳችሁን ማዳን የሚችለውን በውስጣችሁም የተተከለውን ቃል በየዋህነት ተቀበሉ።”
— ያዕቆብ 1፥21
ምክንያቱ ደግሞ “ይህን በመጀመሪያ እወቁ፤ በመጽሐፍ ያለውን ትንቢት ሁሉ ማንም ለገዛ ራሱ ሊተረጉም አልተፈቀደም፤”
— 2ኛ ጴጥሮስ 1፥20 ስለሆነ ነው።
ከዚህ በተጨማሪም በምድር ስንኖር መመሪያችን: መመርመሪያችን: መማሪያችን: እውነትን ሐሰትን የምንለይበት:ቤተ ክርስቲያን የምትተዳደርበት በአጠቃላይ ለአማኞች የመጨረሻው ባለ ስልጣን ነው።
ማንም ይሁን ምንም ይሁን የትኛውም የእግዘብሔር ሰው ሆነ የትኛውም መገለጥ የትኛውም አስተሳሰብ ሆነ የትኛውም ፍልስፍና ከዚህ መፅሐፍ ስልጣን ስር ስለሆነ በዚህ የእግዚአብሔር ቃል ይመዘናል በዚህ የእግዚአብሔር ቃል እውነት መሆኑ ይረጋገጣል።
ስለዚህ ቃሉን በሙሉ ስልጣኑ ተቀብለን: ልንገዛለት ይገባል
የትኛውም ትምህርት አስተሳሰብ ልምምድ በዚህ መፅሐፍ መዝነን ልንቀበል ይገባል
ለቃሉ ስልጣን እንገዛ! ቃሉን እንታዘዝ! ሁሉንም በቃሉ እንመዝን!
የእግዚአብሔር ቃል(መፅሐፍ ቅዱስ) ባለ ስልጣን መፅሐፍ ነው!
. ክፍል ሁለት
@Focusonch
@Focusonc
172 views17:57