2022-07-28 16:53:43
ስነ ፍጥረት
ክፍል ፬ ( አራት)
#የዕለተ_ሰኞ ፍ_ጥራታት
ሰኞ በግዕዝ “ሰኑይ” ሲባል ይህም ሁለተኛው ዕለት ነው በእለተ ሰኞ አዲስ ፍጥረት አልተፈጠረም፡፡ በዕለተ እሁድ የፈጠረውን ከሰማይ እስከ ምድር የነበረውን ውሃ ለሶስት ከፈለው ዘፍ 1፡6-8 በሁለተኛው ቀን ውሀን ወደታችና ወደላይ ለየ በመካከሉም ጠፈርን አደረገ በዚህ ቀን ጠፈርን ብቻ ፈጠረ ኩፋሌ 2፡9 ከጠፈር በላይ የቀረው ውሃ ሀኖስ ሲባል ከጠፈር በታች የቀረውን ደግሞ ውቅያኖስ ይባላል፡፡ ጠፈር ከመፈጠሩ በፊት ከምድር እስከ ኤረር ድረስ ውሀ ሞልቶ ነበር ሰኞ በአንደኛው ሠዓት ሌሊት በውሃና በውሀ መካከል ይለይ ዘንድ ጠፈር ይሁን ብሎ ቢያዝ በዓለም ሞልቶ የነበረው ውሀ ለሦስት ከፈለው፡-
1 ሀኖስ
2 ጠፈር
3 ውቅያኖስ ናቸው፡፡
እግዚአብሄር ከጠፈር በላይ ያወጣው ውሀ ሐኖስ የተባለውን ጠፈርን እንደይጫነው ባቢል የሚባል ነፋስ ወደ ላይ አውጥቶ ሐኖስን አሸከመው ባቢልም የረጋ ነፋስ ነው ጠፈርን ከታች ባቢልን (የረጋ ንፈስ) ከላይ አድርጎ ሁሉን በየቦታው አፀናቸው፡፡ ሐኖስ የተባለው ውሀ ከላይ ጠፈርን ባያቀዘቅዘው ኖሮ የፀሐይ ትኩሳት ይሰብረው (ይበሳው) ነበር፡፡
ሐኖስ፣ ጠፈር፣ ውቅያኖስ እያዳንዳቸው በቤተክርስቲያን ምሳሌ አላቸው
#ሀኖስ፡- በአብ ይመሰላል ምክንያቱም እግዚአብሔር አብን አላየነውም አልዳሰስነውም እንዲሁ ሀኖስም አይታይም አይዳሰስምና ነው፡፡
#ጠፈር፡- በመንፈስ ቅዱስ ይመስላል ይህ በተለምዶ ሠማይ የምንለው ነው፡፡ በመንፈስ ቅዱስ መመሠሉም መንፈስ ቅዱስ በሠው አድሮ ይታያል ነገር ግን አይዳሰስም ጠፈርንም እናየዋለን እንጂ መዳሰስ አይቻልም እግዚአብሔር ጠፈርን ማለትም በተለምዶ ሰማይ የምንለውን ፈፅሞ ነጭ ወይም ቀይ አላደርገውም ይህም ነጭ ቢሆን የሰውን ዓይን ይበዘብዛል ቀይ ደግሞ ቢሆን ዓይንን ያሳውር ስለነበር የሚሰማማ ቀለም አድርጎታል፡፡
#ውቅያኖስ፡- ሲሆን መሬት ላይ እንደመገኘቱ ምሳሌነቱ የወልድ ነው፡፡ ወልድ ስጋ ለብሶ በምድር አይተነዋልና በዚህ ይመሰላል ሶስቱም አንድ ውሃ መሆናቸው ደግሞ “ሥላሴ” ምንም እንኳን በአካል ሶስት ቢሆኑም በመለኮት አንድ መሆናቸውን ያሳየናል እንዲሁም ውሀ በሁሉም ቦታ እንደሚገኝ ሥላሴም በሁሉ ስፍራ የመገኘታቸው ምሳሌ ነው፡፡
#ዕለተ_ሰኞ_የተፈጠረው_የጠፈር_ጥቅም
እግዚአብሔር አምላክ በዕለተ ረቡዕ “ዘይኩኑ ብርሃናት ውስጠ ጠፈር ሰማይ ወያብርሁ ዲበ ምድር” ብርሃን ይሁን ባለ ጊዜ ፀሐይ፣ ጨረቃ፣ ከዋክብት የሚፈጠሩ ናቸውና ለነዚያ ማመላለሻ ሊሆን አስቀድሞ ፈጠረው
ቅርፁ ጎበብ ያለ በመሆኑ ከመጠን ያለፈ የፀሐይ ሙቀት መፋጀት እንዲያቀዘቅዝ
የሠው ልጅ ሰማይን እያየ ሰማያዊ ርስቱን ተስፋ እንዲያደርግ ነው፡፡
#የዕለተ_ማክሰኞ_ፍጥረታት
ማክሰኞ በግዕዝ ሰሉስ ማለት ሲሆን ሰሉስ ማለት 3ኛ ቀን ማለት ነው በዚህች ዕለት 3 ፍጥረታት ተፈጥረዋል፡፡ እነርሡም
1) #አትክልት - በእጅ የሚነቀሉ (የሚለቀሙ)
2) #አዝርእት - በማጭድ የሚታጨዱ
3) #ዕፅዋት - የሚቆረጡና የሚላጡ
እዚህ ጋር ሳናነሳው ማለፍ የሌለብን የዕለተ ሠሉስ ፍጥረታት አራት ናቸው ይላል መፅሐፈ ኩፋሌ፡፡ በዕለተ ሰሉስ ሦስት ፍጥረታት ተፈጠሩ የሚሉ ሊቃውንት በዕለተ እሁድ 8 ፍጥረታት ተፈጠሩ ይላሉና ጨለማን በመደመር መፅሐፈ ኩፋሌ ግን በዕለተ እሁድ 7 ፍጥረታት ተፈጠሩ ስለሚል ጨለማን በመቀነስ የዕለተ ሠሉስ ፍጥረታት ደግሞ 4 ፍጥረታት ስለሚል በጠቅላላው ፍጥረታት 22 ናቸው በማለት ይስማማሉ የዕለተ ሠሉስ ፍጥረታት 4 የሚሆኑት እንዴት ነው ቢባል 1) አዝርእት 2) አትክልት 3) እፅዋት 4) በገነት ያሉ አትክልት ናቸው በማለት የዕለተ ማክሰኞ ፍጥረታትን አራት ያደርገዋል፡፡ እነዚህ የማክሰኞ ፍጥረቶች ለሰው ልጆች መገልገያ ይሆኑ ዘንድ ተፈጥረዋል፡፡
መጠለያ ሠርተን ከቀን ሐሩር ከሌሊት ቁር እንከለልባቸዋለን
ታንኳ/ መርከብ/ በመስራት ባሕር ከመስጠም እንድንባቸዋለን
ቢበርደን አቃጥለን እንሞቃቸዋለን፣ ዕቃ ቢጠፋብን አብርተን እንፈልግባቸዋለን
ምግበ ስጋ እንዳርጋቸዋለን
ልብስ ሰርተን እንጠቀምባቸዋለን
#ከአራቱ_ባሕርያት_ተፈጥረዋል_መፈጠራቸው_በምን_ይታወቃል_ቢሉ_በግብራቸው
#ከእሳት፡- እንደ ተፈጠሩ እንጨት ለእንጨት ባሳበቁዋቸው ጊዜ እሳት ይወጣቸዋል
#ከውሀ፡- እንደ ሆኑ ደግሞ ሲቆርጡዋቸው ደም የሚመስል ይፈሳቸዋል ሌላ እንደ ወተት እንደ ውሃ ያለ ነገር ይወጣቸዋልና
#ከነፋስ፡- አየር የተስተካከለ ይሆን ዘንድ አስፈላጊ ናቸው
#ከመሬት፡- ቆርጠው በጣሏቸው ጊዜ ፈርሰው በስብሰው አፈር ሆነው ይቀራሉ
#ከነዚህ_ከአፈጣጠራቸው_አንፃር_ምሳሌነታቸው_ስንመለከት
1) በሥራቸው 2) በጎድናቸው 3) በጫፋቸው የሚያፈሩ
1. #በሥራቸው_የማያፈሩ፡- ሥር የጌታ ምሳሌ ሲሆን ፍሬው ልደቱን፣ ጥምቀቱን አምነው ክብር የሚያገኙ የምእመናን ምሳሌ ነው “አነ ውእቱ ጉንደ ወይን” ዮሐ 15፡5 እ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናቸው እንዲል፡፡
አንድም በሥራቸው አፍርተው ፍሬያቸውን ከወፍ ከጠላት ሸሽገው የሚያስቀሩ በዚህ ዓለም ሲኖሩ ብዙ ትሩፋት ብዙ ምግባር ሰርተው አብልተው አላበላንም አጠጥተው አላጠጣንም፣ አልብሰው አላለበስንም እያሉ ክብራቸውን ሰውረው በወዲያኛው ዓለም የሚጠቀሙት የባለመቶ ክብር አምሳል ናቸው፡፡ ማቴ 25፡34-40
1. #በጎድናቸው_የሚያፈሩ፡- የሐዋርያት ምሳሌ ናቸው፡፡ ፍሬው ሐዋርያት ያስተማሩትን ትምህርት፣ ያደረጉትን ተአምራት አምነው ክብር የሚያገኙ በውሀ ተጠምቀው በመስቀሉ የፀኑ ፍሬአቸውን ከአዕዋፍ ሰውረው የሚኖሩ ናቸው ማቴ 7፡16
1. #በጫፋቸው_የሚያፈሩ፡- የጌታ ምሳሌ ናቸው ፍሬው ጌታ ያስተማረውን ትምህርት ያደረገውን ተዐምራት አምነው ክብር የሚያገኙ የምዕመናን ምሳሌ ናቸው፡፡ አንድም በጫፋቸው አፍርተው ፍሬያቸውን ወፍ ጠርጥሮት ጠላት ለቅሞት የሚቀሩ በዚህ ዓለም ብዙ ትሩፋት ብዙ ምግባር ሠርው ይታይልኝ፣ ይሰማልኝ፣ ይታወቅልኝ ብለው በከንቱ ውዳሴ ተነድተው በወዲያኛው ዓለም ሳይጠቀሙ የሚቀሩ አምሳል ናቸው ከአንድ መሬት ወይንና ሙዝ ሬትና መርዝ ይበቅላሉና እንዲሁም ከአንድ አዳም ሀጥህ እና ፃድቅ ተገኝተዋል፡፡ እነዚህም ታላላቅ ፍሬን፣ መካከለኛ ፍሬን፣ ጥቃቅን ፍሬን ያፈራሉ ጌታችንም በጎልማሳነቱ፣ በወጣትነቱ፣ በህፃንነቱ ዘመን ለሰራቸው ትሩፋቶች ምሳሌ ናቸው፡፡
#በሚያፈሩበት_ወቅት_አንፃር_ምሳሌነታቸው
• ክረምት ለምልመው በጋ የሚደርቁ በዚህ ዓለም በልተው ጠጥተው በወዲያኛው አለም የማይጠቀሙ የእነ ነዌ አምሳል ናቸው ሉቃ 16፡ 19
• ክረምት ደርቀው በጋ የሚለመልሙ በዚህ አለም ተርበው፡፡ ታርዘው መከራውን ተቀብለው በወዲያኛው አለም የሚጠቀሙ ሰዎች አምሳል ናቸው፡፤ የእነ አልዓዘር አይነቱ ሉቃ 16
96 views13:53