2022-08-24 08:11:16
❖ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምን ማለት ነው ? ~
1 ኦርቶዶክስ የሚለው ስም ከየት የመጣ ነው?
2 ተዋህዶ የሚለውስ ከየት የመጣ ነው?
3 ክርስትያን ማለትስ ምን ማለት ነው???
ኦርቶዶክስ ማለት ቃሉ የግሪክ ሲሆን አማርኛው
ትርጉሙ እውነተኛ፤ቀጥተኛ መንገድ የሆነች ሃይማኖት
ማለት ነው፡፡
ቀጥተኛዋ መንገድ ጠይቁ በእርሷም ላይ ሂዱ
ለነብሳቹሁም እረፍት ታገኛላቹሁ፡፡[ኤር 6÷16]
ነብዩ ኤርምያስ እንዳለው እዚህ ላይ እንግዲህ ቀጥተኛ
ማለት ኦርቶዶክስ ማለት ሲሆን መንገድ ማለት ደግሞ
ሃይማኖት ማለት ነው፡፡
ኢየሱስም ክርስቶስም አለ እኔ መንገድ እውነት
ሕይወት ነኝ ብልዋል፡፡[ዮሐ 14÷6]
ይህ ማለቱም የሃይማኖት መሰረታ ቹሁ እኔ ነኝ ማለቱ
ነው፡፡
ከሰማያዊው ጥሪ ተከፋዮች የሆናቹሁ ቅዱሳን ወንድሞች
ሆይ የሃይማኖታችንን ሊቀ ካህን የሆነውን ኢየሱስ
ክርስቶስን ተመልከቱ፡፡[ዕብ 3÷1]
ስለዚህ ኦርቶዶክስ ማለት ይህ ነው፡፡
2 ተዋህዶ ማለትስ ከየት የመጣ ነው?
ተዋህዶ ማለት ተዋሃደ ከሚለው የግእዝ ግስ
የተወሰደ ሲሆን ትርጉሙ አንድ ሆነ መለኮትና ስጋ አንድ
ሆነ ማለት ነው፡፡ ከሁለት አካል አንድ አካል ፤ከሁለት
ባህርይ አንድ ባህርይ ሆነ ማለት ነው በሌላ አካሄድ ደግሞ
ተዋሃደ ማለት መለኮት ስጋ ለበሰ ከድንግል ማርያም
ከስጋዋ ስጋ ከነብሷ ነብስ ነሳ ማለታችን ነው፡፡
ይህም ደግሞ ግልፅ የሆነ እውነት ነው፡፡
በጀመርያ ቃል ነበረ ፤ቃልም በእግዚአብሔር ዘንድ
ነበረ፤ቃልም እግዚአብሔር ነበረ፡፡[ዮሐ 1÷1]
ቃልም ስጋ ሆነ፤ፀጋንና እውነትን ተመልቶ በእኛ አደረ
እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡[ዮሐ1÷14]
ስለዚህ ተዋህዶ ስንል ቃል ስጋ ለበሰ ማለታችን ነው፡፡
በበለጠ ደግሞ ብርሃናዊው የሆነ የዓለም ብርሃን
ቅዱስ ጳውሎስ ቃል በቃል ተዋህዶ የሚለው ፅፎልናል፡፡
ክርስቶስ እርሱ ሰላማችን ተውና፤ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ
የተነገረለት በራሱ አዲስ ሰውን ይፈጥር ዘንድ ሰላምም
አደረገ፡፡[ኤፌ 2÷14-15]
ስለዚ ተዋህዶ ማለትም ይህን ይመስላል፡፡
3 ክርስቲያን የሚለውስ ከየት የመጣ ነው?
ክርስትያን ማለት ከክርስቶስ ስም የተወሰደ ሲሆን
ክርስቶስ ተከታዮች፤አማኞች ማለት ነው፡፡
ክርስቶስ አምላክ ነው፤ጌታ ነው፤ፈጣሪ ነው፤ፈራጅ ነው
ብለን የምናምን ክርስትያን ተብለን እንጠራለን፡፡
የክርስቶስ ሐዋርያትም በአንጾክያ ምክንያት ክርስቲያን
ተባሉ፡፡[ሐዋ 11÷26]
በትዕቢት ተነፍቶ በዲያብሎስ ፍርድ
እንዳይወድቅ፤ሰው ሁሉ አዲስ ክርስቲያን አይሁን፡፡
[1ኛ ጢሞ 3÷16]
ክርስቲያን እንደሚሆን ግን መከራን ቢቀበል ስለዚህ ስም
እግዚአብሔርን ያመስግን እንጂ አይፈር፡፡
[1ኛ ጴጥ 4÷16]
ስለዚህ ሁሉም ከመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተነሳ ነው፡፡
ኦርቶዶክስ ነው ሃይማኖቴ ስን ቀጥተኛ ናት
ሃይማኖታችን እያልን ነው፡፡
=>የተዋህዶ ልጆች ነን ስንልም የክርስቶስ ልጆች ነን
እያልን ነው፡፡
=>ክርስቲያን ነን ስንልም ክርስቶስን የምናመልክ
የምናምን ክርስቲያን ነን፡፡
ማለታችን ነው፡፡
ሌላው እምነት ፤ሃይማኖት ግን ጴንጤ ፤ፕሮቴስንት
፤ካቶሊክ፤ጆባዊስትን ክርስቲያን ነን ቢሉም እነዚህ
የመሳሰሉ ግን ከጥንትም ያልነበረ ስም አዲስ ድርጂት
ነው በመፅሐፍ ቅዱስም አንድም ቦታ ላይ የለም፡፡
ከግዜ ቡሃላ ከኦርቶዶክስ ወጥተው ወደ ምንፍቅና
የተመሩ ድርጅቶች ናቸው፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ግን ከጥንት የነበረች የነብያት
የሃዋርያት የቅዱሳን ሰማዕታት ሃይማኖት ናት ፡፡አሁን እስከ ልጅ ልጅ ለዘላለም ትኖራለች፡፡
❖አንድ ጌታ❖ እንዲት ሃይማኖት ❖አንዲት ጥምቀት
❖ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዘላለም ትኑር አሜን
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር ይቆየን
291 views05:11