Get Mystery Box with random crypto!

ፍኖተ ~ ጽድቅ

የቴሌግራም ቻናል አርማ fenote_tsedek — ፍኖተ ~ ጽድቅ
የቴሌግራም ቻናል አርማ fenote_tsedek — ፍኖተ ~ ጽድቅ
የሰርጥ አድራሻ: @fenote_tsedek
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.62K
የሰርጥ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።
ይህ ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች የሚተላለፍበት መንፈሳዊ ቻናል ነው። እባካችሁን ይከታተሉን ለሌሎች ያጋሩ ።
#በጽድቅ_መንገድ_ላይ_ሕይወት_አለ።
#በጎዳናዋም_ሞት_የለም። ምሳሌ 12፥28
ሌሎችንም ይጋብዙ ➟ @fenote_tsedek
ለመልዕክት እና ለአስታያየት➟ @fenote_tsedekbot

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-09-01 10:46:38 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን።

#ኖላዊ_ኄር

ኖላዊ ኄር ማለት መልካም እረኛ ማለት ነው። እረኛ እራሱ አይነት አለው መልካምም መጥፎም እረኛ አለ። ነገር ግን ለመልካሙ እረኛ ያለን መረዳት ከህይወት ወስትናችን ጋር የሚገናኝ ነው። ምስንያቱም ስለእረኛችን ማወቅ እና እረኛችንን ማወቅ እጅግ በጣም የተለያዩ ነገሮች ስለሆኑ። ስለእረኛችን ስናውቅ ስለእርሱ የሆነ መረጃ ይኖረናል ማለት ነው እረኛችንን ማወቅ እርሱን መረዳት እና እርሱን መከተል ማለት ነው።

እረኞች አደልበው ለመሸጥ ይጠብቃሉ እርሱ ግን ተሽጦ ሊገዛን ይጠብቀናል፣ እረኞች ሲርባቸው ሊበሉ ይጠብቃሉ እርሱ ግን ምግብ ሆኖ ሊያጠግበን ይጠብቀናል፣ እረኞች እየገረፉ ይጠብቃሉ እርሱ እየተገረፈልን ይጠብቀናል፣ እረኞች በገንዘብ ገዝተው ይጠብቃሉ እርሱ ግን በደሙ ገዝቶን ይጠብቀናል፣ እረኞች በድካማቸው እያረፉ ይጠብቃሉ እርሱ ግን ያለእንቅልፍ በትጋት ይጠብቀናል፣ እረኞች ዋጋ እየተከፈላቸው ይጠብቃሉ እርሱ ዋጋ እየከፈለ ይጠብቀናል፣ እረኞች ወደ ልባቸው መሻት ያሰማራሉ እርሱ ግን ወደ ለምለሙ ስፍራ ያሰማራመፈናል ጌታችን እርሱ በእውነት ኖላዊ ኄር ነው።

የምናውቃቸው እረኞች ሁሉ ከኋላ እየተከተሉ የሚመሩ ናቸው እውነተኛው እረኛችን ግን ከኋላ እያስከተለን ነው የሚመራን። የሚመጣብንን ጦር ከፊት ሆኖ ይመክታል፣ የሚወረወረውን ቀስት እርሱ ችሎት እኛን ያሻግረናል፣ ለእኛ የመጣውን ግርፋት እኔ አለው ብሎ ይገረፋል፣ ችግሩን ሳናይ ማለፍ እንድንችህ እርሱ ከፊት ሆኖ ሁሉን ይቀበላል። ከቶም ብቻችንን ሊተወን የማይችል እውነተኛ እረኛ እርሱ እግዚአብሔር ነው።

እረኛ ከሆነ ክፉ ነገር መናጋውን የሚጠብቅ ነው ክፉ ነገር በሌለበት ወይም ምንም አይነት ክልክላ ባለተሰጠበት ስፍራ የእርኛ መኖር ትርጉም ያጣል። ይህ ዓለም በሞላው በክፉ እንደ ተያዘ እናውቃለን(1ኛ ዮሐንስ 5፥19) ክፉ በሞላባት በዚች ምድር ከክፉ ማምለጫው እረኛችን ነው። ይህም እንደሌሎቹ ለጥቅሙ የሚጠብቀን እረኛ ሳይሆን ለጥቅማችን የሚጠብቀኝ እሩሩ እረኛ። እረኛ ሺ መልካም ቢሆን በጉን ላያርደው ይችላል እንጂ ለበጉ አይታረድም፣ እረኛ ሺ ደግ ቢሆን በጉን አይሸጠው ይሆናል እንጂ ለበጉ አይሸጥም። እውነተኛ እረኛ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ግን ተሽጦ የገዛን ታርዶ ያተረፈን ነው።

መቅበዝበዛችንን የገታ፣ መጥፋታችንን ያገኘ፣ መታረዳችንን የታረደ እርሱ ኖላዊ ሄር ነው ስሙም እግዚአብሔር ነው።
“እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል።” 1ኛ ጴጥሮስ 2፥25 ።
“መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።” ዮሐንስ 10፥11

#ወስብሃት_ለእግዚአብሔር

ዲያቆን ተስፋ መሠረት
ነሐሴ 26/2014 ዓ.ም

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
635 views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:08:42 ከኃጢያት ጋር አትጫወት/አትጫወቺ!! <<>>

አሁን አሁን ከኃጢአት ጋር በጥቂቱ ከመጫወት አልፎ ኃጢአትን እንደውሃ የሚጠጣበት ደረጃ ላይ ተደርሷል ብንል ማጋነን አይመስለኝም። ብዙ ሰው ኃጢአትን መፍራት አቁሟል። ከዚህም የተነሣ በስውር የሚደረጉ የኃጢአት ልምምዶች በምዕመኑ ዘንድ ብቻ ሳይሆን በአገልጋዩም ዘንድ እንደ አሽን ፈልተዋል።

በነገራችን ላይ እግዚአብሔርን የሚፈራና መንፈሳዊ የሆነ ሰው የአደባባይ ህይወቱና የጓዳ ህይወቱ አይለያይም። ፈሪሃ እግዚአብሔር በልቡ ላይ ስላለ በዙሪያው የሚያዩት ሰዎች ኖሩም አልኖሩም እሱ የሚያውቀው አይኖቹ እንደ እሣት ነበልባል የሆኑለት ጌታ ሁልግዜ እንደሚያይ ነው። ከኃጢያት ጋር ምን አለበትና ምን ችግር አለው በሚል የሰነፎች ብሂል ተጠምደን አንድና ሁለት እያልን ጨዋታዎች ከጀመርን አደጋ ላይ መሆናችንን መረዳት አለብን።

የኃጢያት ደሞዝ ሞት ነውና። የኃጢያት ልምምድ እንደ ዘር ሲሆን እንደቀልድ የገባንበትና የጀመርነው ጉዳይ መዘዙ ምናልባት ከአመት በኃላ ይሆናል የሚገለጠው። ዛሬ ዛሬ ማንም አያቅውም ብለን እንደ ጨዋታ የምንለማመደው ኃጢያት ነገ ላይ ኃፍረትንና ውርደትን በአደባባይ ሊያከናንበን ይችላል።

ወዳጆቼ ሆይ ስውር የኃጢያት ልምምዶች በጨለማው አለም ተፅዕኖ ሥር የመሆናችን ምልክት ስለሆነ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ታጥበን ከዚህ ክፉ ባርነት በፍጥነት ልንፈታ ይገባናል። ከሁሉ የባሰው ደግሞ በኃጢያት ልምምድ ውስጥ ያለ የትኛውም ሰው በጥልቁ አለም ላይ የሚሠሩትን ርኩሳን መናፍስቶች ወደ ህይወቱ በቀላሉ መጋበዙ ነው። ምክንያቱም እነዚህ ክፉና ጨካኝ መናፍስቶች ንብረታቸው ባለበት ቦታ ሁሉ የመገኘት ህጋዊ መብት አላቸው።

ንፅህና በጎደለው ቤት ውስጥ ዝንቦች፣ ትኋኖች፣ አይጦች፣ ቅማሎች፣ በረሮዎች፣ ሽረሪቶች ወዘተ እንደሚንፈላሰሱበት እንዲሁ በኃጢያት ወደ ተበከለና ወደ ቆሽሽ የሰው ህይወትም ርኩሳን መናፍስቶችና አጋንንቶች ሳይጠሩ(ተስበው ብቻ) ይመጣሉ። እንደዚህ አይነት ሰዎች በጨለማው አለም ቁጥጥር ሥር ስለወደቁ ከፍተኛ አደጋ ተጋርጦባቸዋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ደግሞ በስውር ኃጢያትን የሚለማመድ ሰው ክፉ መናፍስቶችን የሚቃወምበት ኃይል የለውም። በምሳሌ ለማስረዳት ያህል:-'ሣንባን በእጅ ይዞ ድመትን ለማባረር እንደመሞከር ብላችሁ አስቡት' ሰይጣን ወደሰዎች ህይወት ውስጥ ገብቶ ለመበጥበጥ እና ለማጥፋት ሲፈልግ ቅድሚያ የኃጢያት ግብዣውን በማቅረብ ሲሆን ግብዣውን የተቀበሉለት ሰዎች ደግሞ የፈለገውን እንዲያደርግ ህጋዊ መብትን/ፈቃድን የሰጡት ሰዎች ናቸው።
/ካነበብኩት/

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
1.2K views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 09:19:42 #ሰው_ነህ

ሰው እንጂ ድመት አይደለህምና በሰጡህ ቦታ አትቅር ።

ሰው እንጂ ውኃ አይደለህምና ወደ ተመቸህ አትሂድ።

ሰው እንጂ ውሻ አይደለህምና ወደ ተፋኸው አትመለስ።

ሰው እንጂ ዝንጀሮ አይደለህምና ለፍትወትህ አትኑር።

ሰው እንጂ ጦጣ አይደለህምና ብልጠት አታብዛ።

ሰው እንጂ እባብ አይደለህምና ተንኮለኛ አትሁን።

ሰው እንጂ የመስኖ ውኃ አይደለህምና
ማንም ወደ ፈለገው አይቀይስህ።

ሰው እንጂ ጎርፍ አይደለህምና በቁጣ የሠራኸውን አታፍርስ።

ሰው እንጂ ዛፍ አይደለህምና በወደቅህበት አትቅር።

ሰው እንጂ እህል አይደለህምና ዘረኛ አትሁን።

ሰው እንጂ እንስሳ አይደለህምና ማስተዋል አይራቅህ።

ሰው እንጂ እስስት አይደለህምና አሰመሳይ አትሁን።

ሰው እንጂ ሰይጣን አይደለህምና በሰው ውድቀት ጮቤ አትርገጥ።

ሰው እንጂ መስታወት አይደለህምና ከፊትህ የቆመውን ሁሉ አትምሰል።

ሰው እንጂ መኪና አይደለምህና ማንም ወደ ፈለገው አይንዳህ

ሰው እንጂ ቁስ አይደለህምና ገንዘብ አይለካህ


ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
1.6K viewsedited  06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 07:16:30 የዕለቱ መልእክት

“ትካዜህን በእግዚአብሔር ላይ ጣል፥ እርሱም ይደግፍሃል፤ ለጻድቁም ለዘላለም ሁከትን አይሰጠውም።”

መዝሙር 55፥22

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
1.8K views04:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 21:05:37 “በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው" ማቴዎስ 17፥4

በዬት እየሆንን ነው ያለነው? እኛ የሆኖበት ያ ስፍራ የእኛ ደስታ ስለሆነ በዛ ሆንን ወይስ ለእኛ መልካም ስለሆነ ነው? እስኪ እራሳችንን እንጠይቅ የት ነው እየሆንን ያለነው? ሞልቶ አይሞላ እያልን እየጎደልን ይሆን...? እግዚአብሔር መሃሪ ነው እያልን በድፍረት ኃጢአት ተጠምቀን ይሆን..? ለስጋ ደስታ የዘላለሙን ደስታችንን እየጠፈለቅን ይሆን..? ለምድር ድሎት ከእረፍታችን አየራቅን ይሆን..? ምድር እውቃን ሰማይ ያላወቀን ሆነን ይሆን..? እስኪ ያስደስተናል የምንለውን ነገር ሁሉ እናስበው በእውነት ያ ደስታ ወቀሳ የሌለው ደስታ ነው?

ለእኛ መልካም በሆነ ስፍራ ውስጥ ደስታችን በሙላት አለ። ያስደስተናል ባልነው ነገር ውስጥ ግን አንዳንዴ መልካም ካለመሆንም አልፎ ኃጢአት ሊኖር ይችላል። እኛ ደስታችን በክርስቶስ መሆን አለበት ለዛ ነው ቅዱሱ ቃል ሁሌ በጌታ ደስ ይበላችሁ የሚለን። በዚህ መሆን ደስታዬ ነው የምንለው የት ስንሆን ነው? በእውነት ነፍሳችን የሚያስደስታት ደስታ በእግዚአብሔር መገኘት ውስጥ መሆን ብቻ ነው። የክርስቶስ ክብሩ በሚገለጥበት፣ አብ ስለልጁ በሚመሰክርበት፣ የቅዱሱ መንፈስ ህልውና በሞላበት በዛ መሆን ደስታችን ከመሆኑም ባለፈ መልካማችን ነው።

እግዚአብሔር ያለስፍራ ገደብ የሚገኝ፣ ያለ እድሜ ቁጥር የሚኖር፣ ያለ ወሰን የሚከብር፣ ያለ ከፍታ የሚገለጥ አምላክ ነው። በህይወታችን እንዲገለጥ ክብሩ የኑኗአችን አላማ እንዲሆን ክርስትናችን ያስገድደናልና በዚህ ልክ መልካም የሆነልንን ማወቅና መረዳት የማስተዋል ሁሉ ዋና ነውና ይህ አይወሰድብን። ያኔ በዚህ መሆን፣ በእግዚአብሔር ህልውና ውስጥ መሆን ለእኔ መልካም ነው የማለትን ድፍረት እናገኛለን።

ዲያቆን ተስፋ መሠረት
ነሐሴ 13/2014 ዓ.ም

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
2.0K views18:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 10:11:38 እግዚአብሔር በዙፋኑ አለን?

በህይወታችን ብዙ ልክ ያልሆኑ ነገሮች ተፈጥረው ይሆናል። የተፈጠርነው ለመከራ እስኪመስለን ህይወታችን ጥዕም አልባ ሆኖብን ይሆናል። ምድር ከሰማይ ጋር ተደበላልቆብን ይሆናል። አንዳንዴ ደግሞ በመከራችን ውስጥ ሆነን እግዚአብሔርን እንፈትነዋለን። የመከራችን ብዛት አፋችን እግዚአብሔርማ በዙፋኑ የለም እንድንል በሮችን ይከፍትልን ይሆናል። ብዙ ሰዎች ገጥመውኝ ያውቃሉ በልጆቻቸው ላይ የሚደርሰው መከራ የእግዚአብሔርን መኖር ያጠራጠራቸው፤ በህይወታቸው የተከሰተው ፈተና በእግዚአብሔር ላይ ያላቸውን ተስፋ ያሟጠጠባቸው፤ ለክፉዎች ሲሳካ፣ ለተንኮለኞች ሲሰምር፣ ለሌቦች ሲደላደል፣ አመጸኞች ከፍ ሲሉ፣ ተሳዳቢዎች መሪ ሲሆኑ ሲያዩ አንዳንድ ሰዎች አንተማ የለህም የለህማ ሲሉት ይሰማሉ።

ሰዎች ከደረሰባቸው ነገር የተነሳ እግዚአብሔር የለም ሲሉ ከመስማት በላይ ልብን ዝቅ የሚያደርግ ነገር አይኖርም። የሌለውን እንዲኖር ያደረገ የለም ሲባል መስማት በእጅጉ ለጆሮ ይፈትናል። የመከራችን ብዛት የእግዚአብሔር መኖር መወሰን ከጀመረ እጅግ ሰነባብቷል። ስለተፈተንን የለም እግዚአብሔር ያልንበት ችግር ስለተፈራረቀብን እምነታችን የሻከረብን ብዙዎች ነን። አንድ ነገር ግን ማስተዋል አለብን በኑሯአቸው ብዙ የተሳካላቸው፣ ቅንጦት ምቾት የነሳቸው፣ ገንዘባቸው ደስታ የሚሰጣቸው፣ ዝናቸው ክብር ይሆነላቸው፣ ምድር አላኝ የምትለውን ሁሉ የራሳቸው መድረግ የሚቀላቸው፣ ሰው እንዲኖረው የሚመኘውን ሁሉ ያላቸው ነገር ግን ትልቁን እግዚአብሔር በህይወታቸው የሌላቸው ብዙ ያለቸው ግን ምንም የሌላቸው ምስኪን ፍጥረታት ምድር ላይ ሞልተዋል።

ጠላት በህይወታችን ብዙ ፈተና የሚያመጣው እግዚአብሔር ላይ ያለንን እምነት ለመደርመስ እና አፋችን እግዚአብሔርን ለመሳደብ ዝግጁ እንዲሆን ለማድረግ ነው። ታስታውሳላችሁ ሰይጣን ኢዮብን የፈተነብን ክስተት? እግዚአብሔር ለሰይጣኑ ስለኢዮብ ሲመሰክር እንዲ አለ "በምድር ላይ እንደ እርሱ ፍጹምና ቅን፥ እግዚአብሔርንም የሚፈራ፥ ከክፋትም የራቀ ሰው የለም”(ኢዮብ 2፥3) በዚህ ጊዜ ሰይጣን ይህን አለ "ነገር ግን አሁን እጅህን ዘርግተህ አጥንቱንና ሥጋውን ዳብስ በእውነት በፊትህ ይሰድብሃል አለው። እግዚአብሔም ሰይጣንን፦ ሕይወቱን ተወው እንጂ እነሆ፥ እርሱ በእጅህ ነው አለው። (ኢዮብ 2:5-6) ይህ ክፍል ግርም ይለኛል ኢዮብ ለመከራ ተላልፎ የተሰጠው በእግዚአብሔር ፍቃድ ነው በእርሱ የደረሰው መከራ እግዚአብሔር እንዲሳደብ የሚጋብዘው ቢሆንም በዛ ፈተና ውስጥ ግን እግዚአብሔር አለመሳደቡ እግዚአብሔር ከእርሱ የሚጠብቀው ነገር ነው።

በመከራችን ውስጥ እግዚአብሔር አለ ብለን እንድንቀጥል ተፈልጎ ስንት ጊዜ ለፈተናዎቻችን ወዳቂ ሆነን እግዚአብሔር የለም ብለን ይሆን? ስንቶቻችን እግዚአብሔር ከእኛ ለሚፈልገው የጸና እምነት ጸንተን ይሆን ስንቶቻችን አለ ለምንለው እግዚአብሔር መኖር ምስክሮች ሆነን ይሆን? በችግሮቻችሁ ውስጥ ከችግሮቻችሁ አልፋችሁ አሻጋሪውን አስቡ። መኖራችሁ በአኗሪው ነውና መኖሩ አያጠራጥራችሁ። እግዚአብሔርን እንድትሰድቡት ወደ እናንተ ለመጣ ፈተና ወዳቂ እንዳትሆኑ። የእግዚአብሔርን መኖር ከመጠራጠር የከፋ በሽታ በፍጹም የለም። በሌላ በየቱም በሽታ ብትያዛ አዳኙ እግዚአብሔር ነው እግዚአብሔር የለም በሚል በሽታ የተያዝክ እንደሆነ ማነው አትራፊህ ማነው የሚደርስልህ? ነገ ለማታየው መከራ ብለህ ከመፈጠርህ በፊት ያየህን እግዚአብሔርን አትካደው።

እግዚአብሔር በማይናወጥ ዙፋኑ የነበረ፣ ያለ እና የሚኖር ዘላለማዊ አምላክ ነው። አሜን

ዲያቆን ተስፋ መሠረት
ነሐሴ 12/2014 ዓ.ም

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
2.2K views07:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-14 21:43:26 #ትሻገረዋለህ

በፊትህ ተደቅኖ አላልፈውም ያልከውን፣ በሃይልህ እና በችሎትህ የማትሻገረውን፣ እንዴት ይሆን ብለህ ግራ የተጋባህበትን፣ ጠላት ባሳደድህ ጊዜ ፊትህ የተደቀነብህን፣ በአዕምሮ ልታስበው ታክቶህ ተስፋ ያጣህበትን፣ የአለመቻል ጥጉ ይሄ ነው ያልከውን፣ ከፊትህ ከቆመው መከራ የተነሳ ልክ ያልነበርክበትን ጊዜ ያስናፈቀህን ያንን መከራ እግዚአብሔር ያሻግርሃል። የገጠመህ ምንም ሊሆን ይችላል ከገጠመህ ነገር በላይ ግን የሚያሻግርህን አስበው። በእግዚአብሔር ፊት የቱ ተራራ ደልዳላ ሜዳ አልሆንም ይላል? የትኛም በህር የሱ የሆኑት ያሰምጣል? የትኛም ችግር ፈቺውን ይክዳል? የቱስ መከራ የሱ አቅም ይፈትናል? አንተ አለሁበት የምትለው ፈተና በእግዚአብሔር ፊት ምንም ነውና አሻግሮህ እንደታሪክ እንድትናገረው ያደርግሃል። ከዚህ ነው ያተረፈኝ እያልክ የእግዚአብሔር ድንቅ ስራ ትመስክረበታለህ። እግዚአብሔር አንተን ካለህበት ችግር ለማውጣት ዘወትር መዳፉ የተዘረጋ ነው። ችግሮች አቅማቸውን የሚያጡት ፈቺያቸው እግዚአብሔር ጋር ሲመጡ ነው። ለአንተ ካባድ የመሰለህ ነገር ለአንተ እንጂ ለአባትህ ለእግዚአብሔር ቀላል ነው።

የሀሳብ ምንጭ : ኢየሱ ምዕራፍ 4

ዲያቆን ተስፋ መሠረት
ነሐሴ 6/2014 ዓ.ም

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
2.2K viewsedited  18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-04 09:50:13 #እንግዶች

እንግዳ ለሄደበት ቤት ጊዜያዊ እንጂ ከራሚ ሊሆን አይችልም፡፡ የቆይታ ጊዜው በጨመረ ቁጥር እንግደነቱ ተረስቶ የቤቱ አባል ተደርጎ ሊታሰብ ይችላል፡፡ በዚህ ርዕስ ዉስጥ አንባቢው እንዲረዳ የሚፈለገው አንድም እንግዳ መሆኑን እናም እንግዳ አለመሆኑን ነው፡፡ ለምትኖርበት የእናት የአባትህ ቤት እንግዳ ነህ ብትባል በፍፁም ልብህ ይህን ሊቀበል አይችልም ምክንያቱም ያ ቤት የእንድነት ቤትህ ሰይሆን የመኖርያህ ስፍራ ነው፡፡ ይህቺ የምንኖርባት ምድር የኑሮ ዘመናችን የሚፈፀምባት ብትሆንም ግን የመኖሪያ ስፍራችን ሳትሆን በእንግድነት የመጣንባት ስፍራ ናት፡፡ ብዙ ሰው ግን ሲኖር እንግዳ እንደሆነ አስቦ አይደለም የሚኖረው፡፡ እንግዳ ለሆነባት ምድር ድንበሬ ተነካ ቅጥሬ ተዘለለ ብሎ በየ ክሱ ስፍራ ይባዝናል፡፡

ጳውሎስ ሃገራችን በሰማይ ነው (ፊሊ 3፡20) ያለው ምድር ሃገራችን እንዳልሆነች ተረድቶ ነው፡፡ ምድር ሀገር የምትሆነው ምንም አይነት ሰማያዊ ተስፋ ለሌለው ብቻ ነው፡፡ እርሱ ሁልሙ እና ግቡ ምድር ምድር የሚሸት ስለሆነ የሰማዩን ማሰብ ሞኝነት ይሆንበታል ለዚህም ነው በምድር እና በውስጧ ላሉት በመገዛት ለዘላለም ከሚሆነው ነገር የሚጎደለው፡፡ መፅሐፍ በዚህ የምትኖር ከተማ የለንም (ዕብ 13፡14) በማለት እንግደነታችን ያስረግጥልናል፡፡ እንግዳ በእንግድበት በገባበት ቤት አመፀኛ እንደማሆን፣ በነፍስ አጥፊነት እንደማይሰማራ፣ የክስ መዝገብ እንደማይከፍት፣ ምላሱ እንደሚቆጠብ፣ ድርጊቱ በልክነት እንደሚታጀብ እንዲሁ የሰው ልጅ ሁሉ በምድ ላይ ላለው ኑሮ እንዲ ሊሆን ይገባዋል ማለት ነው አሊያማ ይህ ከቀረ እንግደነቱም መቅረቱ ነውና ማስተዋል ያሻል፡፡ ይህቺን ምድር ልክ እንደ ዘላለም መኖሪያችሁ መሳል የስህተት ክፍል ነው፡፡ እንግዶች እንግድነታችሁን አስተውሉ እንደ እንግዳ ኑሩ፡፡

ለምድር እንግዶች ከሆንን ነዋሪ የሆነው ለማን ነው? ጥያቄውም ሊጠቁም እንደሚፈልገው ነዋሪነታችን ለሰማይ ነው፡፡ የእግዚአብሄር መንግስት የቅዱሳን መሰብሰቢያ እና የሰው ዘር በሙሉ ቢሰበሰብት ልትጠብ የማትችል መንግስት ናት፡፡ እስኪ በማስተዋል ይህን ቃል ያንብቡ በእርሱ ስራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሄር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና ምፃተኞች አይደላችሁም፡፡ (ኤፌ 2፡18-19) ይህን የሰማይ የነዋሪነት መብትን የሰጠን የኛ መሻት እና ትጋት አይደልም ይልቁንም ይህን መብት ያገኘነው ክርስቶስ በከፈለልን ትልቅ ዋጋ ምክንያት ነው፡፡ ከዚህ የተነሳ የእግዚአብሄር መንግስት መኖሪያችን እንጂ ከቶም እንግዳ የምንሆንባት ስፍራ አይደለችም፡፡ በዚች ምድር እንደ ነዋሪ መኖር ልክ ሊሆን እንደማይችል ሁሉ በላይ ባለው መንግስት እንደ እንግዳ መሆን ትክክል ሊሆን አይችልም።

በምታልፈው ምድር እንደ እንግዳ ሰው እንደሆን በማታልፈው መንግስት እንደ ነዋሪ እንደሆንን እንድንረዳ እግዚአብሔር ማስተዋሉን ያድለን። አሜን

ዲያቆን ተስፋ መሠረት
ሐምሌ 28/2014 ዓ.ም

ይቀላቀሉ ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
3.3K views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 20:45:59 #ከመጽሐፍት_አለም

ነፍስ አትሞትም። እርሷ ስለ ዘላለም ሕይወት ወይም ስለ ዘላለም ቅጣት ለዘላለም ትኖራለች። ነፍስ የሕይወቷ አስገኒ ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር የምትለያይ ከሆነ በቅጣት ትኖራለች። እኛ ነፍሳችንን የምንከብርና ከፍ ከፍ የምናደርጋት ከሆንን ስጋዊ ፍላጎታችንን መተው ቀላል ነገር ነው።

መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ "እነሆ የእግዚአብሔር መንግስት በመካከላችሁ ናት"(ሉቃ 17:21) ብሎናል። አይሁድ ይሹት የነበረው ምድራዊውን መንግስት ነበር፤ ክርስቶስ በልባችን ውስጥ የገነባው ግን ዘላለማዊ መንግስት ነው። ስለሆነም ንጹህ መሆን ከፈለጋችሁ ውስጣዊው ሰዋችሁን በመመልከት ለነፍሳችሁ ድህነት ጥንቃቄ አድርጉ።

ወደ ልባችሁ ውስጥ ተመልክታችሁ ለውስጣዊው ሰዋችሁ በእውነት የምትታገሉ ከሆናችሁ፤ ሕይወታችሁን በእግዚአብሔር እጆች ላይ የምትጥሉና በልባችሁ ውስጥ ላለው ለመንፈስ ቅዱስ ስራ ምላሽ የምትሰጡ ከሆናችሁ፤ በዓለም ውስጥ እጅግ ደስተኛዎቹ ሰዎች ትሆናላችሁ! ጉዳዩ ይህ ከሆነ በማንኛውም ስጋዊ ምኞት ወይም ርኩሰት ፈጽሞ ልትሸነፉ አትችሉም። ስለዚህ ንጽሕናን በሕይወታችሁ ውስጥ በሚገኙት በሁሉም ሁኔታዎች ላይ ተግባራዊ ታደርጉታላችሁ።



#ርዕስ: ወጣቶችና የንጽሕና ህይወት
#ጸሐፊ፡ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ
#ገጽ: 20 እና 21



ይቀላቀሉን ➟ @fenote_tsedek
በቅንነት ያጋሩ ➟ @fenote_tsedek
3.0K views17:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 17:47:07 Dhaamsa guyyaa

Ilmi Waaqayyoos akka dhufee fi wanta dhugaa taʼe akka beeknu hubannaa akka nuuf kenne ni beekna; Innis isa dhugaa taʼe keessa qabna, innis ilma isaa Iyyasuus Kiristoos dha. Inni Waaqa dhugaa fi jireenya bara baraa dha. Ijoollee, waaqolii tolfamoo irraa of eegaa.

1Yoh 5:20-21

Join godhaa ➟ @fenote_tsedek
Share godhaa ➟ @fenote_tsedek
2.3K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ