Get Mystery Box with random crypto!

ክፍል (44) #ነገረ ድኅነት #ሰው በበደሉ ምክንያት ያ ተወስዶበት የነበረው ዘለዓለማዊው ሕይወት | ሐረር ፈለገ ሕይወት ሰ/ት/ቤት

ክፍል (44)
#ነገረ ድኅነት
#ሰው በበደሉ ምክንያት ያ ተወስዶበት የነበረው ዘለዓለማዊው ሕይወት የዘለዓለም #ክብርና ነፃነት ተድላና #ሰላም #ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ በተዋህዶ ሰው ሆኖ #ወደዚህ ምድር በመምጣት #በፈቃዱ በተቀበለው
ጸዋትወ መከራና #ሕማም በፈጸመው #የድህነት ተግባር የተመለሰለት ቢሆንም
#ይህን ለመውረስ #ማመን #መታመን #መመስከር ይጠበቅብናል ።
#የክርስትና #መገለጫዎችም እነዚህ ናቸው።
#በክርስትና ሕይወት ሃይማኖትና ምግባር አይነጣጠልም #በሃይማኖት የእግዚአብሔርን #ህልውናና #የማዳን ሥራ አምነን እንቀበላለን ።
#በምግባር ደግሞ ለአመነው እግዚአብሔር እንታመናለን።
( ያዕ 2 ÷ 14 )
ሰው #ለአምላኩ የሚያቀርበው ግብሩ የሚገዛበት ዓይነቱና መታወቂያው ፍትወቱንና (ፍላጎት )
#ጉልበቱን በሚሰጥበት ምግባር (ሥራ ) ነው እንጂ #የጉልበት ድካም የሌለበትን ያቺን የልብ ሃይማኖት ብቻ ይዞ (ኢየሱስ ጌታ ነው እያሉ #በመጮህ የሚዞሩትንና ዕምነት በልብ ነው
እያሉ ከጾም ጸሎት የተራቋቱትን ማለታችን ነው) ።
#ምግባር የማይሠራ ሰው #በፈጠረው በአምላኩ የሚቀልድ
#ሥጋውን የሚወድ ብልጥ አምናለሁ ግን #አልገብርም የሚል ዐመፀኛ መሆኑን ማወቅ የገባዋል።
#የአፍ ሀብታም #የምግባር ድኃ ከመሆን አምላክ በቸርነቱ ይጠብቀን።
ስብሐት ለሥላሴ
ይቀጥላል
ቀሲስ ጥሩውኃ ክፍሌ።