Get Mystery Box with random crypto!

Fasil Yenealem

የቴሌግራም ቻናል አርማ fasilyenealemofficial — Fasil Yenealem F
የቴሌግራም ቻናል አርማ fasilyenealemofficial — Fasil Yenealem
የሰርጥ አድራሻ: @fasilyenealemofficial
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.52K
የሰርጥ መግለጫ

በYouTube ይከተሉን https://youtube.com/channel/UCMZjC5_LoEjS8FxGQOmnrag
ለአስተያየት፣ ለጥቆማ @fasilyenealembot ይጠቀሙ

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-28 22:25:53 ሰበር መረጃ
የኤርትራ ፕሬስ ኤጀንሲ ባወጣው መረጃ መሰረት
የህወሃት አዲስ ወረራ ስትራቴጂ ተደርሶበታል !!

የኤርትራ የስለላ ተቋም በህወሃት ሚስጥራዊ ስብሰባ ላይ በመገኘት የህወሃትን ቀጣይ የወራራ ስትራቴጂ ደርሶበታል። ወረራው በቀጣዩ የክረምት ወቅት የሚጀመር ሲሆን ወረራውን የሚያካሂደው በኤርትራ እና በአማራ ክልል በበለሳ እብናት ጎጃም አቅጣጫ መሆኑን ነው።

ይህን እቅድ ለመተግበር በአማራ ክልል የሃይማኖት ግጭት መፍጠር እና በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የኦሮሞ፣ የአገውና የቅማንት ቅጥረኞችን ግጭት እንዲቀሰቅሱ በመስራት ላይ መሆኑን ተደርሶበታል።

ህወሃት በኤርትራ ላይ ከባድ ወረራ በማድረግ የሱዳንን ኮሪደር ለማስከፈት ጫና ለመፍጠር ማሰቡ ተደርሶበታል።

Via ኤርትራ ፕሬስ ኤጀንሲ
4.2K viewsedited  19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-15 22:56:23 ጠ/ሚ አብይ " አማራ ኦሮሞ የሚሉ ጄኔራሎችን አንፈልግም" እንዳሉት ሁሉ፣ "አማራ ኦሮሞ የሚሉ የክልል መሪዎችንም አንፈልግም" ቢሉ፣ ኢትዮጵያ የብሄር ፖለቲካን "ቻው" ብላ ሰላሟን ታገኝ ነበር። በአንድ አገር ውስጥ የፖለቲካ አመራሩ በብሄር እያሰበ፣ መከላከያውን በብሄር አታስብ ማለት ከባድ ነው። የፖለቲካ አመራሩ ከብሄር አስተሳሰብ ከወጣ፣ መከላከያውም በፍጥነት ከዚሁ አስተሳሰብ ይወጣል። መከላከያ ፖለቲካውን ይከተላል እንጅ፣ ፖለቲካ መከላከያውን አይከተልም። እናም አሁን መከላከያ ላይ የተዘራው ዘር ጥሩ ፍሬ እንዲይዝ ከተፈለገ፣ የፖሊቲካ አመራሩ በመላ ከብሄር አስተሳሰብ ይውጣ።
5.0K views19:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-13 17:13:19 በዚህ ወቅት የሚካሄድ "የግፋ በለው" ፖለቲካ፣ አገርንና ራስን አደጋ ላይ ከመጣል ውጭ፣ የሚያስገኘው ትርፍ የለም። በተለይ የኦሮሞና የአማራ ብሄርተኞች በይዋጣልን የፖለቲካ አካሄዳቸው፣ የታሪካዊቷን አገር ምሰሶ እየነቀነቁ እንደሆነ ልብ ያሉት አይመስልም ። ቀደምቶቻቸው ያስረከቧቸውን አገር ካላፈረስናት ብሎ ልፊያ፣ የጤና አይመስለኝም።

ትናንት የመጣንበት መንገድ ለዛሬ አይሆነንም። የዛሬው መንገድ፣ እንቁላል በአናቱ ላይ ተሸክሞ እንደሚራመድ ሰው፣ በጥንቃቄ የሚሄዱበት እንጅ፣ ድንጋይ ተሸክሞ፣ "ቢወድቅም መሬቱ አይጎዳም" ብሎ በግዴለሽነት እንደሚራመድ ሰው የሚጓዙበት አይደለም።

ኢትዮጵያ በውስጥና በውጭ ጠላት ተይዛ ነፍስ ውጭ ነፍስ ግቢ ላይ በምትገኝበት ሰዓት፣ ጉልኮስ እንኳን ማቀበል ባንችል፣ ተጨማሪ ህመም ባለመሆን ብንተባበር፣ ለፈውሷ እንዳገዝናት ይቆጠራል።

ሁሉም ይስማ። ብሄርተኞችም ሰከን በሉ። መንግስትም አይንህን ግለጥ፤ ጆሮህን ክፈት።
4.7K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-10 23:38:10 በዶ/ር አብይ ላይ ካሉኝ ቅሬታዎች አንዱ፣ ምናልባትም ዋናው፣ ሌብነትንና ሌባን ለመከላከል ከወሬ በዘለለ እርምጃ መውሰድ አለመቻሉ ነው። ምናልባት አብዛኛው ሌባ ሆኖበት ተቸግሮ ይሆናል። ወይም ጊዜ እየጠበቀ ይሆናል። ወይም እንደ መለስ ዜናዊ የፖለቲካ ታማኝነትን ለማግኘት ሲል ሌቦችን አይቶ እንዳላየ እያለፋቸውና ሲያፈነግጡ የስርቆት ካርዳቸውን ለመምዘዝ አስቦ ይሆናል ። ወይም የስርቆት መከላከያ መንገዱ ጠፍቶበት ይሆናል። ወይም ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም ብሎ ንቆት ይሆናል ። ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን፣ ዶ/ር አብይ ባለፉት አራት ዓመታት ብሄር፣ ሃይማኖት፣ ታማኝነት፣ ምህረት ወዘተ ሳይል ሌብነት ላይ ሰይፉን ቢያነሳ ኖሮ፣ አሁን የሚታዩት ችግሮች ቢያንስ አርባ በመቶ ይቀንሱ ነበር። ህዝቡም ጆሮ በመቁረጥ ይተባበረው ነበር። የግጭቶችና የኑሮ ውድነት መንስኤዎችን ብንተረትራቸው የሚያደርሱን የሌብነት ስር ላይ ነው።

ለነገሩ ካመኑበት አሁንም አልረፈደም።
4.1K views20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 11:13:15 በዚህ ወቅትም ይሁን በማንኛውም ጊዜ፣ ኢትዮጵያ ልትጣላት ቀርቶ ልታስቀይማት እንኳ የማይገባ አገር ብትኖር፣ ኤርትራ ናት። ኤርትራ የሰሜን እዝ በተመታ ጊዜ ከዋለችው ውለታ በተጨማሪ ሱዳንና ግብጽ አብረው ሊያጠቁን በተነሱበት ጊዜ፣ ከጎናችን ተሰልፋ እውነተኛ ወዳጅነቷን አሳይታናለች። የኤርትራ መንግስት የቱንም ያክል ዋጋ ያስከፍለው፣ ያመነበትን ነገር ያለምንም ማወላወል ያስፈጽማል፤ የሚነበብ፣ የሚገመትና የሚታመን የውጭ ፖሊሲ ያራምዳል።

ኤርትራ እና ኢትዮጵያ እጣ ፋንታቸው አንድ ስለሆነ ተከባብረውና ተደጋግፈው መጓዝ ምርጫቸው ሳይሆን ግዴታቸው ነው። ኤርትራ በኢትዮጵያ ላይ፣ ኢትዮጵያም በኤርትራ ላይ ቅሬታ ቢኖራቸው፣ ጎረቤት ሳይሰማ ቁጭ ብለው ተነጋግረው መፍታት አለባቸው።

መንግስታችን የሚነበብና የሚታመን የውጭ ፖሊሲ ሊኖረው ይገባል። አንዴ የአፍሪካ ቀንድን እናጣምራለን ስንል፣ ሌላ ጊዜ ፖን አፍሪካኒዝም እናራምዳለን ስንል እንደገና ምዕራባውያን ደጅ ሄደን ስንለማመጥ ስንታይ፣ ሌሎች አገሮች እኛን አምነው ለመከተል ይቸገራሉ። ጠላቶቻችንም ይንቁናል። የውጭ ፖሊሲያችን፣ የአስር፣ የሃያ፣ የሃምሳ ዓመት እየተባለ ሊቀረጽ ይገባዋል። በዘላቂነት የማንፈጽመውን አጀንዳ በስሜት ተነድተን ወይም ለአጭር ጊዜ የፖሊቲካ ትርፍ ብለን፣ ለአንድ ሳምንት አንስተን በሁለተኛው ሳምንት ላይ አንጣለው። ከልብ ያመንበትን አጀንዳ ብቻ ይዘን እስከመጨረሻውን እንጓዝ።

በግሌ በአፍሪካ ጥምረት ( በፖን አፍሪካኒዝም) ከልብ የማምን ሰው ነኝ። የዶ/ር አብይ መንግስት ፖን አፍሪካኒዝምን ማቀንቀን ሲጀምር ከልቤ ተደስቼ ነበር፣ ግን መልሶ አቀዘቀዘውና ሃሞቴን አፈሰሰው። አሁን ፖን አፍሪካኒስቶችን ፍለጋ አይኔን ከኢትዮጵያ ወደ ደቡብ አፍሪካ እየወረወርኩ ነው።

ለማንኛውም አፍሪካን ባናጣምር እንኳ ከኤርትራ ጋር እንዳንጣላ መንገዳችን ሁሉ ብልጠትና ጥንቃቄ የተሞላበት ይሁን።
3.9K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-28 23:17:31 ብልጽግና ያካሄዳቸውን ህዝባዊ ስብሰባዎች ተከታተልኳቸው። በመላ አገሪቱ ያለው ህዝብ ተማሯል- በሰላም እጦት፣ በኑሮ ውድነት፣ በሌብነት፣ በስራ እጦት፣ በአገልግሎት እጦት ወዘተ። ፖርቲው ስልጣን በያዘ በ4 ዓመታት ውስጥ ወይም በተመረጠ ሰባት ወራት ውስጥ ህዝቡ በዚህ ደረጃ ከተማረረ፣ እጅግ አሳሳቢ የሆነ ችግር አለ ማለት ነው። ብልጽግና የሰላም እጦቱንና የኑሮ ውድነቱን ችግር ከህወሃትና ከሸኔ ጦርነት እንዲሁም ከኮቪድና ዓለማቀፍ ፖለቲካው ጋር እያያያዘ ምክንያት ለመስጠት ቢሞክር እንኳ፣ ከስርቆትና ከብልሹ የአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚነሳበትን ችግር፣ ምንም ምክንያት ቢያቀርብ፣ ህዝብን በበቂ ሁኔታ ማሳመን የሚችል አይመስለኝም።

ህዝቡ ምሬቱን ገልጿል፤ ምሬትን በማስተንፈስ ደግሞ ትንሽ መጓዝ ይቻል ይሆናል፣ ብዙ ርቀት መጓዝ ግን አይቻልም። መንግስት መጠንቀቅ ያለበት ህዝቡ ወደ " ብንናገር ምን ዋጋ አለው" አይነት ስሜት ውስጥ እንዳይገባ ነው። ህዝብ ወደዚህ ስሜት ውስጥ ከገባ መመለሻ የለውም።

የህዝቡን ቀዳሚ ጥያቄዎች መሬት ላይ በሚታይ ስራ ለመፍታት እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን በፍጥነት ማሳየት ይገባል። በተስፋ የተሞላ ህዝብ ተስፋው የተሟጠጠ ጊዜ የሚያቆመው አይኖርምና።
3.7K views20:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-28 23:14:43 ሕይወት ካለ ብዜት አለ!

ጥቂት ዛፎች ካየህ ጫካ ማየትህ አይቀርም! ጥቂት ወፎች ካየህ አእዋፍ ማየትህ አይቀርም! ጥቂት ሰዎች ካየህ ሕዝብ ማየትህ አይቀርም! ይህ የሚሆንበት ቀላል መርህ ሕይወት ያለውና የሚንቀሳቀስ ነገር ሁሉ የመባዛት አቅም የመኖሩ እውነታ ላይ ነው ፡፡

በእጅህ ያለውን ማንኛውንም ነገር ፣ እውቀት ፣ ገንዘብ ፣ ሃሳብ ፣ ግንኙነት . . . ሕይወት ጨምርበትና አንቀሳቅሰው! መባዛቱና ማደጉ አይቀርም

መልካም ቀን

@eth_tibeb
3.0K views20:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-26 14:06:54 ትክክለኛው የኢሳት ኢንተርናሽናል የዩቱብ ቻናል https://youtube.com/channel/UCMZjC5_LoEjS8FxGQOmnrag
3.1K views11:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-21 20:00:21 ብዙ ሀገራት ዛሬ ሀገር የሆኑት እንደዚህ አይነት ሰው ስላላቸው ነው ኢትዮጵያም ብዙ እንደዚህ አይነት ሰው ያስፈልጋታል



4.8K views17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-05 21:07:38 Facebook በተደጋጋሚ ገፃችንን እየዘጋብን ሰለተቸገርን የቴሌግራም ገፅ ለመክፈት ተገደናል።

አስተውሉ ከዚህ በፊት የቴሌግራም ገፅ ኖሮን አያውቅም ።

ኢሳት የኢትዮጵያውያን አይንና ጆሮ

https://t.me/ESATtvethiopia
4.9K views18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ