Get Mystery Box with random crypto!

የሬጌው👑 ንጉስ🇪🇹™

የቴሌግራም ቻናል አርማ eyobreggae — የሬጌው👑 ንጉስ🇪🇹™ የ
የቴሌግራም ቻናል አርማ eyobreggae — የሬጌው👑 ንጉስ🇪🇹™
የሰርጥ አድራሻ: @eyobreggae
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 219
የሰርጥ መግለጫ

ሴት ልጅ
👉እህት
👉እናት
👉 vetሚስት
👉ልጅ
ነችና ልታከብራት ይገባል
ወንድ ልጅም
👉ወንድምሽ
👉አባትሽ
👉ባልሽ(ውሽማሽ)
👉ልጅሽ
ነውና ልታከብሪውይገባል😂
#መልካም ምኞት መግለጫ
🌼🌼🌼🌼
1 2 3 4 እያልን አንድላይ ተያይዘን የመጣን ውድ ጓደኛዬ❤️❤️
ከመፈጠሬ ጀምሮ እስካሁን ሰአት ጭምር መልካምነታችሁ የበዛልኝ ቤተሰቦቼ💝💝
@ye27lejj

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-04-10 22:05:26 እባካቹ ስሙት
@nahitua19
156 views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-04 07:26:52 የአለማችን ሀብታም የሆነው ቢልጌት አሁን በኤለን መስክ ልበለጥ የቻልኩበት ምክንያት አናዶኛል ሲል ተናገረ
@Nahitua19
216 views04:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-01 16:16:40 የሚኒሊክ ጀብድ የአድዋው ድል የፈረሰኛው ጊዮርጊስ እርዳታ እና ያልተነገረለት ታላቅ ሀያል ያለው ሞኦ መንግስት የተሰኘው መጻህፍ !

ለዛሬቱ የድል በአል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን፡፡

የዛሬ 125 አመት እለተ ቅዳሜ ማታ በአድዋ አቅራቢያ በሚገኘው እምየ ምኒሊክ ባከበሩት የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ታላቅ ሱባኤ ተይዟል ::
ኢትዮጵያ በቀዳማዊ ሚኒልክ ማለትም ከ 3ሺ አመት በፊት ከ እስራኤል ከሌላውያኑ ጋ በሚስጥር የገቡ ታቦተ ጽዮንን ጨምሮ አምስት መለኮታዊ ሀብታት አሏት።
ለዛሬ አንድን ልግለ ጥላችሁ።
በአድዋ ላይ ድል ስላደረገው የጊዮርግስ መገለጥ ሃይሉ ምንጭ ምክኒያት ከዚህው ቅዱስ መጻህፍ የሚቀዳ ታሪክ አለው።
ብዙ ጊዜ በአድዋ ታቦት አብሮ መዝመቲ ቅዱስ ጊዮርጊስም መዋጋቱ ይገለጣል ነገር ግን ዋናው ሚስጥር ሲነገር አይስተዋልም።
''ሞኣ መንግስት'' ይባላል ከታቦተ ጸዮን ጋ ለሙሴ ከተሰጡት መለኮታዊ ስጦታወች ዋናው ነው።
ይህ ቅዱስ እቃ ሀገር ስትጨነቅ መከራ ሲመጣ ቸነፈር ሲፈጠር ክፉ እና ወራሪ ሲመጣ ጠበበት አባቶቻችን ከመንበሩ ያወጡታል ጸሎቱ የሚፈጸምበት የራሱ የሆነ ስርአትን ይፈጸማሉ በሀገር ላይ ፍጹም ሰላም ይመጣል ይህ መፈንቅለ መንግስት እንደ ማለት ነው ሲገለጥ ሲነበብ ስርአቱም ሲፈጸም ሃይሉ ይገለጣል ሚኒሊክም ብልህ ነበርና ሚስጥሩንም ያወቅ ነበር እና ካለበት አስፈልጎ ከመንበሩ አስወጥቶ ስርአቱን እንዲፈጸም አድርጓል ሃይሉም በምድሪቱ ላይ ተገለጠ ያነገሱት ጊዮርጊስም ሊረዳ ከራማ መጣ።

ካህናት በግራና በቀኝ
"ነዓ ነዓ ነዓ ጊዮርጊስ እንዘ ትፄአን በፈረስ ወነዓ ፍቁርየ ዘልዳ እነዘ ትፄአን በፈረስ ወነዓ ፍቁርየ ዘልዳ ንጉስ ......እያሉ ያነ ቫሉ፡፡

ሊቃውንቱ ይዘምራሉ" ጊዮርጊስ ረባን ዘሀገረ ኢትዮጰያ ስህን
ንስእለከ በብርሀን ከመ ትናዝዘነ ነዓ እምክቡደ ሀዘን" ይላሉ..
እምየ ሚኒሊክ የንግስና ልብሳቸውን አውልቀዉ ቃልኪዳናቸውን ከጊዮርጊስ ጋር ሊያደርጉ '' ጊዮርጊስ ሆይ ተራዳን'' እያሉ ከቤተመቅደሱ ፊት ለፊት ታጥቀው ተምበርክከው ይማፀናሉ::
ጀግኒት ጣሂቱ
"አድህነኒ እግዚኦ እምፃርየ
ወአንግፈኒ እም እለ ቆሙ ላእልየ
አቤቱ ከጠላቶቻችን አድነን
በላያችንም ከቆሙት አስጥለን "
እያለች ፈጣሪን ትማፀናለች
፡
፡
እንዳይነጋ የለም ነጋ እምየ ሰራዊታቸውን ሰበሰቡ በአረጋዊው ካህን አሰባረኩ ፤ከሰራዊቱ ጋር በማርያም ስም ተማማሉ፡፡
አድዋ ላይ የዘመተው አሁን አዲስአበባ ያለው የፒያሳውን ጊዮርጊስ በመምህሬ ካሳሁን አስከብረው(አስይዘው ) በጀብድ እና በጀግንነት የልዳውን ጊዮርጊስን ይዘው ወረዱ፡፡
ጦርነቱ ተጀመረ፡
፡
፡
፡
… የአድዋ ጦርነት በ1888 ዓመተ ምሕረት በየካቲት 23 ቀን እሑድ ጦርነት ተዠመረ፡፡ ወዲያው የኢጣሊያ የጦር አዛዥ ያገር ተወላጅን ጦር እፊት አስቀድሞ ሲዋጋ በኋላ የራስ መንገሻና የራስ ሚካኤል የዋግ ሥዩም ጓንጉል ወታደሮች ከበው በጥይት ስለ ቆሏቸው ይበልጦቹ እጦርነቱ ላይ ሞቱ፡፡ ገሚሶቹ ዐውቀው እጃቸውን ሲሰጡ የቀሩት ደግሞ ወዳልተነካው ጦር ወደ ጄኔራል አርሞንዲ ሠራዊት በሽሽት እየሄዱ ተደባለቁ፡፡1050 ኪሎሜትሮችን በባዶ እግራቸው ተጉዘው የጊዮርጊስን ታቦት አክብረው ጣሊያንን ሲዋጉ የነበሩት ካህኑ ካሳሁን የተሸከሙት የልዳው ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ተቀምጦ የጣሊያንን መድፍ ያኮላሻል ፣ታንክ ያከሽፍል የጦር ጀቶችን ከሰማይ ወደምድር ዶጋ አመድ ያደርጋል ፤ በዛን ጊዜ ከአለም የጦር ሜካናይዝ ከፍተኛ የነበሩትን የጣሊያንን ጦር በ 4 ሰአት ውስጥ መድረሻውን አሳጣው፡፡
የኢትዮጵያ የጦር ሠራዊትም እያቅራራና እየፎከረ ወደ ፊት አልፎ ገስሶ ከሚባለው ጉብታ ላይ ደርሶ እንደ ገና ተጋጠማቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ዠግናው ፊታውራሪ ገበየሁ ከሠራዊታቸው ተለይተው ጠላት መካከል ገብተው ከቀኛዝማች ታፈሰ ጋራ እየፎከሩ የጠላትን አንገት በጎራዴ ሲቆርጡ በጥይት ተመተው ወደቁ፡፡
ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ምኒልክ የጦር ወታደራቸውን በሚያበረታታ ቃል ሲያደፋፍሩ እንዲሁም እቴጌ ጣይቱ እንደ ወንድ በጦርነቱ መካከል እየተላለፉ የቆሰለውን ሲያነሱ ለተጠማው መጠጥ ለተራበው ምግብ ሲያሰጡ ዋሉ፡፡ እነሊቀ መኳስ አባተ እነራስ አሉላ እነበጅሮንድ ባልቻ እነደጃች በሻኽ አቦዬና የቀሩትም የጥንት ወታደሮች በመድፍና በጠመንዣ በዠግንነት ሲዋጉ የጠመንዣውና የመድፉ ጩኸት ከልክ ያለፈ ነበር ይላል ታሪክ፡፡
የኢጣሊያንንም ወታደር ከበው እየተፏከሩ በጥይትና በጎራዴ ሲደበድቡት የኢጣሊያ ጦር በዠግንነት አራት ሰዓት ከተዋጋ በኋላ ሽሽት ዠመረ፡፡ በዚህ ጊዜ ኢትዮጵያውያን እየተከተተሉ ሲወጉት አዝማቹ ጄኔራል አልቤርቶኒ ተቀምጦበት የነበረው በቅሎ ተመቶ ወደቀ፡፡ ኢትዮጵያውያን ደርሰውም ጄኔራሉን ማረኩት፡፡
የአንደኛው ክፍል ጦር አዛዡ ተማርኮ ሠራዊቱ በጭራሽ ከጠፋ በኋላ ሁለተኛው ክፍል የጦር ሠራዊት ራአዮ ከሚባለው ስፍራ ላይ ሆኖ ካራት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ የሦስተኛውን ክፍል የጄኔራል ኤሌናን ጦር ጨምሮ ተዋግቶ በመጨረሻ የጦር አዛዡ ጄኔራል አሪሞንዲ እዚያው እጦርነቱ ላይ ሞቶ ተገኘ፡፡
ከዚህም በኋላ በመጨረሻ ያለው የኢጣሊያ ጦር በተለይ ማርያም ሸዊቶ ከሚባለው ስፍራ ላይ ተጋጥሞ ከቀድሞው የበለጠ ጦርነት ተደረገ፡፡ ይልቁንም የመጨረሻው ድል የሚፈጸምበት ለመሆኑ የሁለቱም የጦር ሠራዊት ተደባልቆ በጨበጣ በሚዋጉበት ጊዜ በጨበጣ በሚደረገው ዘመቻ ከኢጣሊያኖች ይልቅ ኢትዮጵያውያን በጎራዴ አነዛዘር የቀለጠፉ ነበሩ፡፡
በዚህ ጊዜ ኢጣሊያኖች ገሚሶቹ ሲሞቱ የቀሩት ደግሞ ወደ ኢትዮጵያውያን ደግነው ይተኩሱበት የነበረውን ብረት አፈሙዙን ጨብጠው ሰደፉን ወደ ሰማይ እየሰቀሉ ተማረኩ፡፡ ድሉም በማያወላውል አኳኋን የኢትዮጵያ ሆኖ ጦርነቱ በ1888 ዓመተ ምሕረት በዚህ በየካቲት 23 ቀን ተጀምሮ በዚሁ እለት በታላቅ ጀግንነት ተፈጸመ፡፡አለምንም ጉድ አሰኘ ለመላው የነጭ ህዝቦች አሁን ሊቀበሉት የሚከብዳቸው ዉረደትን አከናነበ፡፡ እንዴት ሆነ ብለው ዛሬም ድረስ ይገረማሉ ??? የጀርመኑ ፀሀፊ ራይመድ በመገረም ታምር ነው በማለት ፅፎታል፤ አውን ታምር ነው፤በ 1970ወቹ አንድ የጣሊያን ፀሀፊ እንዲህ አለ የሀገሬን የጣሊያንን ወታደር የፈጀው በሚበር በነጭ ፈረስ የሆነ አንድ ሃያል ነው ይህንንም በአይናችን አይተናል ሀይሉም እጅግ ከባድ ነበር ይላል፡፡

እውነትም ለማመን የሚከብድ ታምር በባዶ እግር የተሰራ የሀገር ፍቅር ጀብድ ነው፡፡
አወን አ ድ ዋ፡
፡ የሚኒሊክ የመሪነት ጥበብ ነው፤
የራስ መኮነን ራስነት የተገለጠበት፤
የባልቻ አባ ነብሶ ወኔ የተመ ሰከረበት ፤ ያሉላ አባ ነጋ ጀግንነት የታየበት ፤ የአያቶቻችን የመንፈስና የእምነት ልእልና የተገለጠበት
የጣይቱ የሴትነት እልህ ጥጉ የታየበት፤ የኢትዮያውያን የማንነት አሻራችን በአባቶቻችን ደም ና አጥንት በማይጠፋ የደም ቀለም ተፃፎ በአለም ህዝብ ዘንድ የሚነበብበት ፤የክብርና የጀግንነት ወኔ እና አልደፈር ባይነት የተገለጠበት፤ የድል አጥቢያ የብርሀን ጮራ የታየበት አሁን ላለንበት አንፃራዊ ያልተመረዘ ማንነት ምክኒያት ያ የአድዋ ገድል ነው፡፡
አውን አባቶቻችን አኩረተውናል እኛስ እንዳባቶቻችን በዘመናችን ድል አድርገን ልጆቻችን እናኮራ ይሆን ?????

ይህ ታሪካዊት ኢትዮጵያ ነው ያላችሁን አስተያየት @Abelbalehager ላይ አድርሱኝ።
@ethioabesha
@ethioabesha
@ethioabesha
198 views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-22 06:48:02 #አትወድህም ቢሉህ ውሸታም በላቸው
መዉደድ ማለት ልኩ ፈፅሞአልገባቸው
ግን መውደድ ምንድን ነው?
ፍቅር የሚሉት ጉድ መኖርያው ከየት ነው?
እኔ ምለዉ ዓለሜ
ግን የምር ሲታሰብ ፍቅር እዉነት ጉድ ነው?
እንጃ!
ብቻ የማያቁት አለም ያላዩት ገፅታ
ሲታገሉት ቢውሉ ፍፁም ማይረታ
በልባችን ሀገር ከትሞ የሚኖር
ከራስ ግዞት ዓለም ፈፅሞ ሚያቃቅር
ፍቅር።
#እና እንደነገርኩ
ሺ ነገር ቢነግሩ ፈፅሞ አትስማቸው
በኔና ባንተ ዓለም
ወሬ አይታለም
የሚነገር ሁሉ ሚሰማ አይደለም
አይን ባለቀሰ ልብ ተከፍቶ አያድርም
በውሸታም እሳት ፍቅር አይጎረናም።
#እናልህ…………
ከመውደድም በላይ እኔ አፈቅርሀለው
ላፍቃሪ ምሳሌ በሰብልዬ ምትክ እተካልሀለው
ግና እኔ ሰብለን ሆኜ በእዜር ድርሰት ዓለም
አደራውን ጌታ አንተን በዛብህ አርጎ ይፃፍህ ግድ የለም።
#እናልህ አካሌ
ከሰዎችህ ይልቅ እኔ እሻልሀለው
ፍቅርን ከቃል በላይ ኖሬ አሳይሀለው
አትወድህም ላሉህ ለኚያ ጥላ ቢሶች ጥላ ለሌላቸው
ጥላህ ሆኜ ኖሬ ይክሰም ተንኮላቸው።

( ሰሎሜ መብራቱ )
179 views03:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 22:08:10 +25250940729698Be:
ለማንበብ 15 ደቅቃ ብቻ ስጥ ህይወትን ይቀየራል አትሳሳት
share አድርገው
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
ዓለም ወዴት እየሄደች ነው? 1. - መጽሐፍ ቅዱስን ማቃጠል በኡጋንዳ በይፋ ተረጋግጦአል
* በደቡብ አፍሪካ ውስጥ ፣ ወንድ ወይም ሴት በዝሙት ምክንያት ሌላውን የመክሰስ መብት የለውም
*በአሜሪካ እየታየ ያለው የወንድ ለወንድና የሴት ለሴት ጋብቻ
*ጀርመን ወንድም እህቱን ማግባት እንደሚችል ፣ አባት ልጁን:እናት ልጆአን የማግባት ፍቃድን መስጠቱ ፡፡
*የmiami ከተማበመንገድ ላይ ፣ በቤተ ክርስቲያን ፣ በገቢያ ፣ በእግር ኳስ ሜዳ ወዘተ ውስጥ ወሲባዊ ግንኙነት በማንኛውም መንገድ ማግኘት እንዲችሉ መፍቀዶአ
.*ካናዳ (ከእንስሳት ጋር የ sexታ ግንኙነትን መፍቀዶአ
* በስፔን ውስጥ-የወሲብ ፊልሞች በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና በዩኒቨርሲቲዎች መፈቀዱ *- ለአካለ መጠን ያልደረሱ ዝሙት አዳሪዎች ፈቃድ ማሪ ሉክ በህግ መፈቀዱ *በመጨረሻም ዩኤስ አሜሪካ የሰይጣንን ቤተ ክርስቲያን ከፍታለች ፡፡ በይፋ።
የተከበራችሁ ወንድሞች እና እህቶች ፣ መጨረሻው ተቃርቧል ፣ ጌታ ኢየሱስ በቅርቡ ይመጣል! ማርታናታ!!!
ክርስትያኖች ትኩረታቸው እየተከፋፈሉ ሲሆን ዲያቢሎስ መለኮታዊውን ምህረት ለማስቆም ከፍተኛ ቁጥር ያላቸውን ነፍሳት ከእርሱ ጋር ሊወስድ ይፈልጋል ፡፡ ደቂቃ ካለዎት ... ይህንን መልእክት ያጋሩ ፡፡ ለምን በቤተክርስቲያን ውስጥ እንተኛለን ? ስለ እግዚአብሔር ማውራት ከባድ የሆነው ለምንድነው ሐሜት ለመናገር በጣም ቀላል የሆነው ለምንድነው? የእግዚአብሔርን መልእክት ችላ ማለት ለምን ቀላል ሆነ?
ይህንን መልእክት ለጓደኞችዎ ይልካሉ ወይም ችላ ይላሉ? እግዚያበሔር “በሰዎች ፊት ብትክዱኝ በአባቴ ፊት እክድዳችሁአለሁ” አለ ፡፡ እግዚያበሔር ከወደዱ ይህንን መልእክት ለምርጥ ጓደኞችዎ እና በቡድን በ 60 ሴኮንድ ውስጥ ያጋሩ ፡፡ እግዚአብሔር ይባርኮት. ኣሜን
የአለም መጨረሻ ተቃርቧል አትዘናጉ
አሁን ያለንበት 2013 ዓም + 5500 ዘመን=7513 ስለዚህ ከ 8ኛው ሽ ላይ ቀንሱት ።
8000 – 7513= 487 ዓም ይቀራል።
ነገር ግን ሰምታችሁ ከሆነ ዘንዶ 400 ዓመት ገዝቷል ይባላል እስኪ ጠይቁ።
እና የዘንዶው ሲቆጠር 487 – 400 =87 አመት ቀረው።ትንቢቱም እየተፈፀመ ነው። ሌላው ይህ በንዲህ እንዳለ ደሞ
666 አሁን እዚህ በደጃችን ነው፡፡ አጠንክረን እንፀልይ፡፡ የአውሬው
ቁጥር 6 6 6 የሚፈፀምበት የትንቢት ጊዜ አልቋል/ተፈፅሟል፡፡
የአሜሪካ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ባስተላለፈው የኦባማን የጤና
ሽፋን ረቂቅ በህግ እንዲካተት ተደርጓል፡፡ የህግ ተግባሩ በቅርቡ
ይጀምራል፡፡ ይህን የጤና ሽፋን ረቂቅ በእያንዳንዱ የአሜሪካ ዜጋ
የሰውነት ክፍል ላይ ግላዊ የሬዲዬ ፍሪኩዌንሲ ቺፕስ መልክ (RFID
CHIPS) እንዲተከል ታዟል፡፡ ይህ ቺፕስ በግንባር ወይም በክንድ ላይ
ይደረጋል፡፡ ይህ ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ እንደሚናገረው በራዕይ 13 :
15 -18 የተቀመጠውን የአውሬው ምልክት ይፈፀም ዘንድ ነው፡፡ እና
አሁንም ስለ ፍፃሜው ትጠራጠራለህ? ታውቃለህ ለኦባማ የተለየ
መኪና እንደተሰራ አውሬው የሚባል? ተዘጋጅ ንጥቀት አሁን
ይጀምራል፡፡ ራዕይ 13ን ቀድመው ተጫውተውታል፡፡ ብዙዎች ግን
ይህን አልተገነዘቡትም፡፡ 1. ለምንድን ነው ይህ ችፕስ ከባንክ
አካውንት ጋር የተቆራኘው ወይም የተገናኘው? አስታውሱ መጽሐፍ
ቅዱስ እንደሚለው ካለ አውሬው ቁጥር 666 ልትገዙም ወይም
ልትሸጡም አትችሉም ስለሚል፡፡ እስኪ ገምቱ ይህ ቺፕስ ከገንዘብ
ዝርዝር መረጃ ጋር ለምን ተገናኘ? እንዲያውም በጣም ያሳዘነኝ
በቤተክርስቲያን ያሉ ብዙዎች ሰዎች ጌታ ሲመጣ ይህን ሁኔታ
ሊያልፉት አይችሉም፡፡ ደግሞም ብዙዎቹ መጨረሻው እንደቀረበ
አያውቁም፡፡ የቴክኖሎጂ በጣም መራቀቅ ምክንያት ነው ብላችሁ
መልስ እንዳትሰጡኝ፡፡ በማንኛውም የህይወት ጎዳናችሁ
ከእግዚአብሔር ጋር ካልተስማማ አሁኑኑ ንሰሀ ግቡና ተለወጡ፡፡
ካለበለዚያ መንግስተ ሰማያትን ካጣችሁት ገሀነምን አታጡትም፡፡
ስለዚህ አስቡበት፡፡ ገሀነም መልካም ስፍራ አይደለም በጣም
አስከፊው ክፍሉ እንደ መንግስተ ሰማያት ዘላለማዊነት እንዳለበት
እዚህም እንደዛው ነው፡፡ ጆሮ ያለው ይስማ መንፈስ ለአብያተ
ክርስቲያናት የሚለውን ይስማ፡፡ ጠቃሚ ያልሆነ ነገር ከምትልኩ ይህን
ለሌላው ብታስተላልፉ መልካም ነው፡፡ ለምታውቋቸው ቅርብ
ለሆኗችሁ ሰዎች ላኩላቸው፡፡ እስኪ የወንጌላዊ ስራ እንስራ፡፡
እባካችሁ ለምታውቋቸው ለእያንዳንዳቸው በየስማቸው ላኩላቸው፡፡
ለሞባይል እንደምንጠነቀቅ ያክል ለእግዚአብሔር ቃል ብንጠነቀቅ
ምን እንደሚሆን ልትገምቱ ትችላላችሁ፡፡ ከዚህ ደግሞ በጭራሽ
ልንላቀቅ ነፃ ልንሆን አንችል፡፡ ስለዚህ የቻልነውን ያክል እንትጋ
እንጋደል፡፡ 7% የሚሆኑቱ ናቸው መልዕክቱን የላኩት በድጋሚ 93%ቱ
ግን አልላኩም አላወቁም ስለዚህ ጠንክረን እንስራ፡፡ ሰይጣን
እንዲህ ይላል፡- " የሚገርመኝ ሰው እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ
አይታዘዝም እኔን ይጠላኛል ግን ይታዘዘኛል፡፡" ይህን መልዕክት በኋላ
እንዳትልኩት አሁኑኑ ላኩት!!!

ቢያንስ ለ #15 ሰው
277 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-21 00:47:14 1ኛ . ጠዋት ከእንቅልፍህ ስትነሳ ፈጣሪህን አመስግን

ለሊቱን በዙሪያ ባደሩ መናፍስት በሞት ልትወሰድ ስለነበር

2ኛ ሙሉ አካል ስላለህ

አካልህ ሙሉ ባይሆን እንኳን በጤና አልያም በህይወት ያቆየህ ፈጣሪ ምክንያት ስላለው ነው ለዚህም አመስግነው

3ኛ ቢያንስ በቀን አንዴ እንኳን አፍህን ትሽራለህ ቢኖር መርጠህ በልተህ ባይኖርህ ውሀ እንኳን ጠጥተህ ትውላለህ ለዚህ የፍጥረታት ጌታን አመስግን

4 . በመንገድህ ሁሉ ስትሄድ ሠላምታ እና ትህትና ከአንደበትህ አይራቅ

5. ለሚገጥምህ መጥፎ ነገር ሁሉ ምላሽህ ደግ እና መልካም ነገር ይሁን
ክፉ ተነጋግረህ ክፉ ሰርተህ ከሰውም ከእንስሳውም ከሁሉ ፍጥረት ከምትጣላ ይልቅ ሁሉን እንዳመጣጡ በፍቅር ሸኘው

6. ባረፍክበት ሁሉ እርዳታህን ለሚሻ ሁሉ ደግ ልቦናህን እና ቀኝ እጅህን አትከልክል የዛሬ ቸርነትህ የነገ እረፍትህን ያበጃጃል እና

7. ከማንም ጋር በማይረባ ጊዜያዊ ጥቅም አትጣላ አትጋጭ ችኩል አትሁን ለሚያልፍ ቀን ብለህ ፍፁም አትማረር ይልቅ ይቅር ማለትን ቅድሚ መስጠትን ለልብህ አስተምር ላንተ ያለው እንጀራ ሳይሻግት ሳይደርቅ በለምለምነቱ በጊዜው ከነሌማቱ ቤትህ ይገባልና

8. ህፃናትን ሁሉ በአንድ ልብ ውደድ ሠው ማፍቀርን ሀቀኝነትን እና ደግነትን አስተምራቸው ነገ በድካምህ ጊዜ ሮጠው የሚደርሱልህ እነሱ ስለሆኑ
ወጣት እኩዮችህን አትናቅ አንተ የደረስክበት እንዲደርሱ እርዳቸው ከአንተ የበለጡም ስለሚኖሩ ራስህን ለማሻሻልም የሚረዳህ ቸር ማድረግ ነውና ከፍ ለማለት የሌሎችን ጫንቃ አትስበር እንዲያው እጅ ለእጅ ተያይዞ መለወጥን አስብ
አዛውንቶችን አተጨቁን ምርቃታቸው ርግማናቸውም ከአፋቸው ጠብ አይለምና ከፈጣሪ እንዳትጣላ

''የሚያድግ ህፃን አይጥላህ
የሚሞት ሽማግሌ አይርገምህ''

9. ስላለህም ስላጣኸውም ሁሉ አመስግን ስላሣለፍከው መከራም ስላየኸውም ተድላ በምክንያተ አመስግን የሚሆነው ሁሉ በምክንያት ባንተ ላይ ስለተከናወነ አመስግን ማማረር ከቶ ስለማይበጅ

10. ስላሣለፍከው ቀን ሁሉ ምሽት በቤትህ ለፈጠረህ አምላክ ምስጋናን አቅርብ ብዙዎች አንተ ያየኸውን ቀን ሳያዮ ብዙ እየተመኙ በህይወት ወደማይቀረው አለም አልፈዋልና

።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ክፉ እንድናስብ እንድንፈፅም ከዚያም በራሳችን እንድናዝን እንድንፀፀት የሚያረገን የክፋት አባት እሱ ሠይጣን ነውና እሱን በቸርነት በመልካም ስራና በየእምነታችን በፈጣሪ ምስጋና እንበቀለው እንጉዳው

ከዚህ በላይ ጉዳትና በቀል የለም
ሰው ሳይሆን ሠይጣን ነውና ጠላታችን
በሱ ላይ ነው በቀለኝነታችን




Sh Like are To Ur Frien
@eyobreggae
@eyobreggae
•═••• •••═•
~~~~~~~~~~~~~~
486 views21:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ