2022-08-10 11:38:31
ተሰቀለ ¡ ክርስቲያን: የኢየሱስ ፈቃድ ለኛ ሀጢያት ተቸንክሮ ወዶ እና ፈቅዶ መስዋዕትነት መሆን ነው
መጽሐፍ : መሞት ፈቃዱ አልነበረም ከሞት ያድነው ዘንዳ ይለምን ይማጸን ነበር
“አምናችሁም በጸሎት የምትለምኑትን ሁሉ ትቀበላላችሁ አላቸው።”
— ማቴዎስ 21፥22
“አባ አባት ሆይ፥ ሁሉ ይቻልሃል፤ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን አንተ የምትወደው እንጂ እኔ የምወደው አይሁን አለ።”
— ማርቆስ 14፥36
ሉቃስ 22
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴
³ ከሰማይም መጥቶ የሚያበረታ መልአክ ታየው።⁴⁴ በፍርሃትም ሲጣጣር አጽንቶ ይጸልይ ነበር፤ ወዙም በምድር ላይ እንደሚወርድ እንደ ደም ነጠብጣብ ነበረ።
መዝሙር 34
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ይህ ችግረኛ ጮኸ፥
እግዚአብሔርም ሰማው፥ ከመከራውም ሁሉ አዳነው።⁷
የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል፥ ያድናቸውማል።መዝሙር 142
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ጮኽሁ፤ በቃሌ ወደ እግዚአብሔር ለመንሁ።
…
⁵ አቤቱ፥ ወደ አንተ ጮኽሁ፦ አንተ ተስፋዬ ነህ፥ በሕያዋንም ምድር አንተ እድል ፈንታዬ ነህ አልሁ።
⁶ እጅግ ተቸግሬአለሁና ወደ ልመናዬ አድምጥ፤ በርትተውብኛልና ከሚያሳድዱኝ አድነኝ።
መጽሐፍ: እርሱ መሲሁን ያድነው ዘንዳ ቃል ገብቷል
“በመከራ ቀን ጥራኝ፥ አድንህማለሁ አንተም ታከብረኛለህ።”
— መዝሙር 50፥15
መዝሙር 91 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ በአንበሳና በእፉኝት ላይ ትጫማለህ፤ ደቦሉን አንበሳና ዘንዶውን ትረግጣለህ።
¹⁴ “ወዶኛልና እታደገዋለሁ፤ ስሜን አውቆአልና እከልለዋለሁ።
¹⁵ ይጠራኛል፤ እመልስለታለሁ፤ በመከራው ጊዜ ከእርሱ ጋር እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ፤ አከብረዋለሁ።
¹⁶ ረጅም ዕድሜን አጠግበዋለሁ፤ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።”
“እግዚአብሔር፣
የቀባውን እንደሚያድን አሁን ዐወቅሁ፤ የማዳን ኀይል ባለው ቀኝ እጁ፣ ከተቀደሰው ሰማይ ይመልስለታል።”
— መዝሙር 20፥6 (አዲሱ መ.ት)
“በመከራ መካከል እንኳ ብሄድ፥ አንተ ሕያው ታደርገኛለህ፤ በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጆቼን ትዘረጋለህ፥ ቀኝህም ታድነኛለች።”
— መዝሙር 138፥7
“እርሱ ግን ወደ እነርሱ ተመልክቶ፦ እንግዲህ፦
ግንበኞች የናቁት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ ተብሎ የተጻፈው ይህ ምንድር ነው?” — ሉቃስ 20፥17
መዝሙር 118
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ በተጨነቅሁ ጊዜ እግዚአብሔርን ጠራሁት፤ ሰማኝ አሰፋልኝም።
⁶ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፥ አልፈራም፤ ሰው ምን ያደርገኛል?
⁷ እግዚአብሔር ረዳቴ ነው፥ እኔም በጠላቶቼ ላይ አያለሁ።
…
¹⁷
አልሞትም በሕይወት እኖራለሁ እንጂ፥ የእግዚአብሔርንም ሥራ እናገራለሁ።
¹⁸ መገሠጽስ እግዚአብሔር ገሠጸኝ፤ ለሞት ግን አልሰጠኝም።
…
²² ግንበኞች የናቁት ድንጋይ፥ እርሱ የማዕዘን ራስ ሆነ፤
“አንተ አምላኬ ነህ አመሰግንህማለሁ። አንተ አምላኬ ነህ፥ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ፤ ሰምተኸኛልና፥
መድኃኒትም ሆነኸኛልና አመሰግንሃለሁ።”
— መዝሙር 118፥28
ማቴዎስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወሰደውና እርሱን በመቅደስ ጫፍ ላይ አቁሞ፦
⁶
መላእክቱን ስለ አንተ ያዝልሃል እግርህንም በድንጋይ ከቶ እንዳትሰናከል በእጃቸው ያነሡሃል ተብሎ ተጽፎአልና የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ፥ ወደ ታች ራስህን ወርውር አለው።
መዝሙር 91
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³ እርሱ
ከአዳኝ ወጥመድ ከሚያስደነግጥም ነገር ያድንሃልና። …
¹¹
በመንገድህ ሁሉ ይጠብቁህ ዘንድ መላእክቱን ስለ አንተ ያዝዛቸዋልና፤
¹² እግርህም በድንጋይ እንዳትሰናከል በእጆቻቸው ያነሡሃል።¹³ በተኵላና በእባብ ላይ ትጫማለህ፤ አንበሳውንና ዘንዶውን ትረግጣለህ።
¹⁴ በእኔ ተማምኖአልና አስጥለዋለሁ፤ ስሜንም አውቆአልና እጋርደዋለሁ።
¹⁵ ይጠራኛል እመልስለትማለሁ፥ በመከራውም ጊዜ ከእርሱ ጋራ እሆናለሁ፤ አድነዋለሁ አከብረውማለሁ።
¹⁶ ረጅምን ዕድሜ አጠግበዋለሁ፥ ማዳኔንም አሳየዋለሁ።
“ይህ የሆነ፦
ከእርሱ አጥንት አይሰበርም የሚል የመጽሐፉ ቃል እንዲፈጸም ነው።”
— ዮሐንስ 19፥36
መዝሙር 34
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ጻድቃን ጮኹ፥ እግዚአብሔርም ሰማቸው ከመከራቸውም ሁሉ አዳናቸው።
¹⁸ እግዚአብሔር ልባቸው ለተሰበረ ቅርብ ነው፥ መንፈሳቸው የተሰበረውንም ያድናቸዋል።
¹⁹
የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፥ እግዚአብሔርም ከሁሉ ያድናቸዋል።
²⁰ እግዚአብሔር አጥንቶቻቸውን ሁሉ ይጠብቃል፥ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም።²¹ ኃጢአተኞችን ክፋት ይገድላቸዋል ጻድቃንንም የሚጠሉ ይጸጸታሉ።
²² የባሪያዎቹን ነፍስ እግዚአብሔር ይቤዣል፥ በእርሱም የሚያምኑ ሁሉ አይጸጸቱም።
“እርሱም፦
እላችኋለሁ፥ ከወዴት እንደ ሆናችሁ አላውቃችሁም፤ ሁላችሁ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ይላችኋል።” — ሉቃስ 13፥27
መዝሙር 141
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁹ ከሰወሩብኝ ወጥመድ፥ ዓመፅንም ከሚያደርጉ ሰዎች ዕንቅፋት ጠብቀኝ።
¹⁰ እኔ ብቻዬን እስካልፍ ድረስ ኃጢአተኞች በወጥመዳቸው ይውደቁ።
ማቴዎስ 7
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² በዚያ ቀን ብዙዎች፦ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል።
²³ የዚያን ጊዜም፦ ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።
መዝሙር 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ዓመፃን የምታደርጉ ሁሉ፥ ከእኔ ራቁ፥ እግዚአብሔር የልቅሶዬን ቃል ሰምቶአልና።⁹ እግዚአብሔር ልመናዬን ሰማኝ፤ እግዚአብሔር ጸሎቴን ተቀበለ።¹⁰ ጠላቶቼ ሁሉ ይፈሩ እጅግም ይጐስቍሉ፤ ወደ ኋላቸው ይመለሱ፥ በፍጥነትም ይፈሩ።
“ኢየሱስ በዚህ ምድር በኖረበት ዘመን ከሞት ሊያድነው ወደሚችለው ጸሎትንና ልመናን ከታላቅ ጩኸትና ከእንባ ጋር አቀረበ፤ ፍጹም ትሑት ሆኖ በመታዘዙም ጸሎቱ ተሰማለት።”
— ዕብራውያን 5፥7 (አዲሱ መ.ት)
“መሥዋዕትንና ቊርባንን አልፈለግህም፤ ጆሮቼን ግን ከፈትህ፤ የሚቃጠል መሥዋዕትን፣ የኀጢአትንም መሥዋዕት አልሻህም።”
— መዝሙር 40፥6 (አዲሱ መ.ት)
መዝሙር 51 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁶ መሥዋዕትን ብትወድ ኖሮ ባቀረብሁልህ ነበር፤ የሚቃጠል መሥዋዕትም ደስ አያሰኝህም።
“ሳሙኤልም እንዲህ አለ፤ “ለእግዚአብሔር ቃል በመታዘዝ ደስ የሚለውን ያህል፣ እግዚአብሔር፣ በሚቃጠል ቍርባንና መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ! መታዘዝ ከመሥዋዕት፣ ማዳመጥም ከአውራ በግ ሥብ ይበልጣል።”
— 1ኛ ሳሙኤል 15፥22 (አዲሱ መ.ት)
“ከመሥዋዕት ይልቅ ጽድቅንና ፍትሕን ማድረግ፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት አለው።”
— ምሳሌ 21፥3 (አዲሱ መ.ት)
መዝሙር 86
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁵ አቤቱ፥ አንተ መሓሪና ይቅር ባይ ነህና፥ ምሕረትህም ለሚጠሩህ ሁሉ ብዙ ነውና።
⁶ አቤቱ፥ ጸሎቴን አድምጥ፥ የልመናዬንም ድምፅ ስማ።
⁷ ትመልስልኛለህና በመከራዬ ቀን ወደ አንተ እጠራለሁ።
መጽሐፈ ሲራክ 2:10-11
በዘመን የቀደሙ ሰዎችን አስተውሉ በእግዚአብሔር አምኖ ያፈረ ማነው? እወቁ እሱን በመፍራት መከራውን የታገሠ በመከራ እንደ ጣለው የቀረ ማነው? ለምኖትስ ቸል ያለው ማናው?
የጻድቁን ኢየሱስን ጸሎት ጆሮ ዳባ ብሎት እንዲሰቀል ለጠላቱ አሳልፎ ሰጠው ? ወይስ ከጭንቁ አዳነው !
ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱሏህ ወበረካቱህ
በወንድም ሀቢብ
@ewnet_lehulum
781 viewsedited 08:38