ቅዱስ ሚካኤል:- አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ዐሥራ ሁለት በዚህች ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው:: በዚህች ቀን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ወደ አሞጽ ልጅ ወደ ነቢይ ኢሳይያስ ላከው:: ኢሳይያስም መልአኩ እንደነገረው ይቅርም ብሎት ወደ ይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ ሔዶ እግዚአብሔር ይቅር እንዳለው ከደዌው እንዳዳነው በዕድሜውም ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እንደ ጨመረለት ይነግረው ዘንድ አዘዘው:: ሚስት አግብቶም ምናሴን እስከ ወለደው ድረስ በተጨመረለት ዕድሜ እያመሰገነ ስለኖረ እንዲህ ሆነ:: የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ቸርነት አያችሁን! አብቅቶልአል በቃ ልትሞት ነው ብሎ ብቻ አይተወንም:: መልአኩን ልኮ ይመክረናል:: በተለያዩ መምህራን በተለያዩ የሕይወት ውጣ ውረድ እያባበለ አስተምሮ ይመክረናል:: ሰምተንም በቶሎ ስለ ኃጢአታችን ተጸጽተን ንስሐ ስንገባ በዕድሜአችን ላይ አምስት ዐሥር ዐሥራ አምስት ሠላሳ ከዚያም በላይ ዓመት ይጨምርልናል:: ከእኛ የሚጠበቀ ስለ ሠራናት ኃጢአት መናዘዝ ስለተደረገልን ነገር ማመስገን ብቻ ነው:: በእውነት ፍጹም ፍቅሩን ከእኛ ያላራቀ የቅዱሳኑ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ይመስገን:: ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ በሚካኤል አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን:: @ewkete_orthodox 579 views05:27