ሊቃውንቶች ብዙ ጊዜ ቃለ እግዚአብሔር በብራና እንዲሁም በወረቀት ለመጻፍ ሸምበቆ ቀርጸው ቀርክሃ ቀርጸው እንዲሁም ገቢሩ ባዘዘው እጽዋቶች መጻፍያ በመቅረጽ ብዙ መዛግብቶች ብራናዎች ጽፈው ደጉሰው አስቀምጠዋል:: አሁን ደግሞ ገቢር ካዘዘው ውጭ ከሆነ ዘመኑን የተላበሱ ለፍጥነትም ምቹ ብዙ የማያስቸግሩ እሊህ እና የመሳሰሉት ብዙ የብዕር መጽፍያዎች ተበጅተዋል ::ቢሆንም ግን ቅሉ! ግን ልብ ልንለው የሚገባው ነገር ለመጻፍ ስለተመቸን ብቻ ገቢሩ ካዘዘው መጻፍያ ውጭ በእሊህ ብንጽፍ አይሆንም እና ቅሉ እንጠንቀቅ:: ብዙ መልካም ጥበቦች ሰመሬታ የማጣታቸው ምክያት አንዱ ይህ ነው:: ለምሳሌ በሸምበቆ መጻፍያ:የሴት ቀስት መጻፍያ:የጠምበለል ተቀጽላ መጻፍያ:የዕጸ ሳቤቅ መጻፍያ ወዘተ እያለ ስያዝ በታዘዘው መሰረት ይጻፍ አልያም የተጠቀሱት ዕጽዋቶች በማድረቅ በምላጭ ለመጻፍያ እንዲሆን አድርገን በመቅረጽ መልካም የሆነው የእግዚአብሔርን ጥበብ እንመዝግብ:: ሻሎም ነኝ:: 3.0K views20:13