Point ስልክ ይዞ የተገኘ ተማሪ ስልኩ አይቀማም በቀጥታ ከፈተናው ይወገዳል ፤ ፈተና አይፈተንም ፦ ትምህርት ሚኒስቴር - ሶሻል እና ናቹራል ላይ ላሉ ተመሳሳይ የትምህርት ዓይነቶች የተለያዩ ፈተናዎች ተዘጋጅተዋል - ተማሪዎች ከግቢ በምንም ዓይነት ምክንያት መውጣት አይችሉም - በስህተት እንኳን ስልክ ይዞ የተገኘ ተማሪ ከፈተናው ይወገዳል ፤ ከግቢውም እንዲርቅ ይደረጋል - ተማሪዎቹ አንዴ ካምፓስ ውስጥ ከገቡ በኋላ ከሌላው ዓለም ጋር ግኑኝነት አይኖራቸውም - ግቢ ከገቡ በኋላ ፈተናው ቢወጣ እንኳን ተማሪዎች ሊጠቀሙ የማይችሉበት ሁኔታ ተፈጥሯል - ተፈታኞች በግቢ ቆይታቸው እናበላቸዋለን፣እናጠጣቸዋለን፣እንከባከባቸዋለን፣... ከሌላው ዓለም ግን ግንኙነት የላቸውም - የአንድ አካባቢ ተወላጅ አካባቢው ላይ ያሉ ተማሪዎችን አይፈትንም - ማንኛውም የአንድ ዩንቨርሲቲ አስተማሪ የሚያስተምርበት ዩንቨርሲቲ ውስጥ አይፈትንም 358 views06:41