Get Mystery Box with random crypto!

በትግራይ ክልል በትምህርት ገበታ ላይ ያለው የተማሪ መጠን 41 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገለፀ፡፡ በክል | 🇪🇹ኢትዮ University

በትግራይ ክልል በትምህርት ገበታ ላይ ያለው የተማሪ መጠን 41 በመቶ ብቻ መሆኑ ተገለፀ፡፡

በክልሉ በትምህርት ገበታ ላይ መሆን ከሚገባቸው 2.4 ሚሊዮን ተማሪዎች 994,369 ተማሪዎች (41.1 በመቶ) ብቻ በትምህርት ላይ እንደሚገኙ የህዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የመቐለ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ገልጿል፡፡

ተማሪዎቹ በትምህርት ገበታቸው ላይ ያልተገኙት በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት እንደሆነ ጽ/ቤቱ አስረድቷል፡፡

ጽ/ቤቱ በ22 ወረዳዎች በሚገኙ 794 ትምህርት ቤቶች ላይ በተደረገ ክትትል 112 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ እንደወደሙ፥ 595 በከፊል እንደተጎዱ ጠቁሟል፡፡

794 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ምንም ዓይነት ጉዳት ያልደረሰባቸው 47 ትምህርት ቤቶች ብቻ እንደሆኑ የጽ/ቤቱ ኃላፊ ፀሀዬ አንባዬ ለሸገር ኤፍኤም ተናግረዋል፡፡

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በክልሉ መዲና መቐለ ባደረገው ክትትልም በ24 ትምህርት ቤቶች ተፈናቃዮች መኖራቸውን አረጋግጫለው ብሏል፡፡ #SheferFM

ለ 12ኛ, ለ Remedial እና ለ Freshman ተማሪዎች   ቻናል
https://t.me/+s5S2h_gcBlY0Y2U0
 
            Share share
ለተጨማሪ መረጃ
╔═══════════╗
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
@ethiouniversity1 
╚═══════════╝