2022-01-02 07:08:59
አንብቡት እጅጉን ትገረሙበታላቹ -----------------------------------------------
መስቀል አምላኪዎች(በኢብኑ ሙነወር)
ጎበዝ ክርስቲያኖች የሚያመልኩት ስንት አምላክ ነው? ኢንፍሌሽን እዚያ አካባቢም አለ እንዴ? ስማቸውን ተመልከቱማ፡- ገ/ስላሴ፣ ገ/ማርያም፣ ገ/መስቀል፣ ገ/ሚካኤል፣ ወ/ስላሴ፣ ወ/ማርያም፣ ወ/መስቀል፣ ኃ/ስላሴ፣ ኃ/ማርያም፣ ኃ/መስቀል፣ ኃ/ሚካኤል፣ … መቼም እነሱ እየሱስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ እየተወገረ እንደተገደለ እንደሚያምኑ ይታወቃል፡፡ በርግጥ ይሄ የኛ እምነት አይደለም፡፡ እነሱም እምቢ ብለው እንጂ መፅሀፋቸው “በመስቀል ላይ የሚሞት የተረገመ ነው” ይላል፡፡ ማየት ማመን ነው [ዘዳግም 21፡ 23] ግለጡና አንብቡ፡፡ ለነገሩ እዚያ አካባቢ ማየት ማመን ላይሆን ይችላል፡፡ አሁን ርእሴ ይሄ አይደለም፡፡ ግን እንዳው የሚገርመው የሚያመልኩት ብዛቱ!
1. ሶስቱን ስላሴዎች ያመልካሉ፡፡ ይሄውና ማስረጃው፡-
- “ክርስቶስ ላንተ እንሰግድልሃለን ከሰማያዊ ከቸር አባትህ ጋራ አዳኝ ከሆነ መንፈስ ቅዱስ ጋራ እንሰግድልሃለን… ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስ አንዲት ስግደት እሰግዳለሁ/3 ጊዜ/ ፡፡ አንድ ሲሆን ሶስት፣ ሶስት ሲሆኑ አንድ፣ በአካል ሶስት ሲሆኑ በመለኮት አንድ ለሚሆኑ እሰግዳለሁ” [ውዳሴ ማርያም፤ የዘወትር ፀሎት፡ 7-8]
- “በመንፈስ ቅዱስም እናምናለን እርሱም ጌታ ህይወትን የሚሰጥ ከአብ የሰረፀ ከአብ ከወልድ ጋር በአንድነት እንሰግድለታለን” [ውዳሴ ማርያም፤ የዘወትር ፀሎት፡ 8]
2. ቅድስት ማርያምን ያመልካሉ፡፡ ይሄውና ማስረጃው፡-
- “አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለድንግል ማርያም እሰግዳለሁ፡፡” [ውዳሴ ማርያም፤ የዘወትር ፀሎት፡ 8]
- “እናታችን ማርያም ሆይ ሰላም ላንቺ ይሁን እያልን እንሰግድልሻለን እንማልድሻለን ከአዳኝ አውሬ ታድኝን ዘንድ ተማፅነንብሻል ስለ እናትሽ ስለ ሐና ብለሽ ስለ አባትሽ ስለ ኢያቄም ብለሽ ድንግል ማህበራችንን ዛሬ ባርኪልን” [ውዳሴ ማርያም፤ የዘወትር ፀሎት፡ 10]
3. እልፍ አእላፍ ታቦቶችን ያመልካሉ፡፡ ማየት ማመን ነው፡፡
4. መስቀል ያመልካሉ፡፡ በየእለቱ የምናየው ቢሆንም መጥሀፍ መጥቀሱ አይከፋም፡፡
- “ዓለምን ለማዳን ሲል እየሱስ ክርስቶስ ለተሰቀለበት መስቀልም እሰግዳለሁ፡፡ መስቀል ሀይላችን ነው፡፡ ሃይላችን መስቀል ነው፡፡ የሚያፀናን መስቀል ነው፡፡ መስቀል ቤዛችን ነው፡፡ አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን፡፡ ያመነውም እኛም በመስቀሉ እንድናለን፡፡ ድነናልም” [ውዳሴ ማርያም፤ የዘወትር ፀሎት፡ 8]
- “… ለእየሱስ ክርስቶስ መስቀልም ምስጋና ይገባል፡፡” [ውዳሴ ማርያም፤ የዘወትር ፀሎት፡ 9]
ክርክር እንዳይረዝም ሰጋሁ እንጂ ሌሎችም በተጨባጭ የሚያመልኳቸውን መቁጠር ይቻል ነበር፡፡
ግን እኔን ለጊዜው የበለጠ የገረመኝ መስቀሉ ነው፡፡ አጃዒብ አትሉም!!! አምላካቸው የተሰቀለበትን፣ የተዋረደበትን መስቀል ማምለክ ምን የሚሉት እብደት ነው? ከመስቀሉ ላይ ያሰቃዩት ጠላቶቹ እንኳን ቢያደርጉት ግርምታችን ይቀል ነበር፡፡ ጉራቸው ቢደብርም ከባድ ጠላታቸውን በመገላገላቸው ደስታቸውን ለመግለፅ ነው ሊባል ይችላል፡፡ ምናልባት፡፡ ግን እኮ የተገደለበት መስቀል እንደ ቅዱስ ከታየና ከተመለከ በመስቀሉ የሰቀሉትና ያሰቃዩት ይበልጥ ቅዱሳን ናቸው ማለት ነው፡፡ እነሱ ባይሰቅሉላቸው የሚመለክ መስቀል የለ የሚከበር ስቅለት የለ፡፡ ግን አምላኩ ይቅር፣ ሰው ወንድሙ ወይም አባቱ የተገደለበትን ጩቤ የቤቱን ግድግዳ አሸብርቆበት ብታዩት ምን ትላላችሁ? በኪሱ ይዞት ቢዞርስ? ካንገቱ ላይ ቢያስረውስ? ቢስመውስ? ቢሳለመውስ? ቢሰግድለትስ? እዕምሮው እያለ ሰው ይህን ያደርጋል ተብሎ ይታሰባል? ዘወትር ስለምናየው ለምደነው እንጂ ይሄ እኮ እጅግ በጣም የሚደንቅ ነገር ነው፡፡ ሰው በራሱ ጊዜ በህሊናው ላይ ይሳለቃል እንዴ? ወይ ነዶ! ወዶ አይደለም ለካ ታላቁ ዓሊም ኢብኑ ሐዝም “እኔ አላህ በቁርኣኑ ባይነግረኝና በአይኔ ባላያቸው ኖሮ እንዲህ ዓይነት ሰዎች ይኖራሉ ብዬ አላምንም ነበር” ያለው:: እዚህ ላይ አንድ የህንድ ንጉስ የተናገረውን ባሰፍር አይከፋም:: እንዲህ ነበር ያለው “የሌሎች እምነት ተከታዮች ክርስቲያኖችን ለእምነታቸው ሲሉ ቢፋለሟቸውም እኔ ግን ለህሊና ሲባል ሊፋለሟቸው ይገባል ነው የምለው፡፡ ምንም እንኳን ማንንም በመዋጋት ባላምንም እነዚህን ግን ከዓለም በሙሉ ለይቼ አወጣለሁ፡፡ ምክኒያቱም ነገረ ስራቸው ከህሊና ጋር መፃረር ነውና፡፡ ጥላቸው ከህሊና ጋር ነውና፡፡ …” [ሂዳየቱል ሐያራ፡ 21]
የመሲህ ባሮች ሆይ አንድ ጥያቄ አለን
የተረዳው ካለ መልሱን እንሻለን
ጌታ ግፍ አቅቶት ሰዎች ከገደሉት
አለቀ አከተመ የታል አምላክነት?!
ሰዎች የሰሩትን በሱ ላይ ሲያደርሱ
ጌታ ግብራቸውን ፈቅዶ ነው በራሱ?
እንዲያ ከሆነማ ምንኛ ታደሉ?!
ፍቅሩን ይቸራሉ ፈቃዱን ሲሞሉ::
ባደረሱት ሁሉ አልፎ ከተከፋ
እንግዲህ ምን ይባል?
ሀይሉ ከኮሰሰ ሀይላቸው ከሰፋ?!
ግን እንጠይቃለን ለመልስ አትንፈጉ
ማለባበስ ይቅር ይመለስ በወጉ
ፈጣሪዋን አጥታ ዐለም ስትዋትት
ሰው ወደ ማን ነበር የሚያስበው ፀሎት?
ፍጡር ፈጣሪውን ካፈር ሲያደባየው
ሰባቱን ሰማያት ማን ነበር ያቆየው?
ምስማር ተቸንክሮ ሲያሸልብ ፈጣሪ
አለም ቀርታ ነበር ያለ አስተናባሪ?
የሰማይ መላእክት ምንኛ ለገሙ?!
እጁ ተቸንክሮ ዋይታውን ሲሰሙ?
እንጨቱም ታምር ነው አቅሙ መቋቋሙ
አምላክ ያክል ነገር ችሎ መሸከሙ
ስለቱስ ጭቃኔው ብረቱ ምስማሩ
አካሉን ሰንጥቆ ስቃይ ማሳደሩ
ጉድ በሉ እሄን ጌታ
በአይሁድ የሚረታ
ማጅራቱን ታንቆ ታስሮ የሚመታ
ኋላስ ራሱ ነቃ ከሞት አንሰራራ
ወይስ ጌታ አገኘ ህይወት የሚዘራ?!
ጉድ በሉ ለቀብር ጌታ አቅፎ ለያዘ
የባሰም ሆድ አለ አምላክ ያረገዘ
ዘጠኝ ወር ታሽጎ ሲኖር በጨለማ
ሐይድ እየተጋተ ደም እየተጠማ
ብልት ቀዶ ወጣ አቡሻ ህፃኑ
አፉን ለጡት ከፍቶ አቤት ማሳዘኑ!
አስቡ እሄን አምላክ ሲጠጣ ሲበላ
ከዚያም ያስገባውን ሲያስወጣ በሌላ
ጌታዬ ከፍ አለ ከነሳራ ቅጥፈት
ሁሉም ይጠየቃል ለቀባጠረበት
የመስቀል ባሮች ሆይ ግራ ገባኝ እኔ
ይህን ማሽቀንጠሩ ፅድቅ ነው ኩነኔ
ማቃጠል ሰባብሮ ፈቃጁን ጨምሮ
ህሊና ከዚህ ውጭ ይፈርዳል አምሮ?
አምላክ አቅም አንሶት ለተጠፈረበት
ሰብሮ እንደማቃጠል ጭራሹን አምሎኮት?!
እውነትም እርጉም ነው ለምንስ ይዘንጋ
በመሳለም ሳይሆን በእግር ይሰጥ ዋጋ!
ለተዋረደበት ጌታህ ከነነፍሱ
አንተ ካመለክከው የሱ ነህ የነሱ?
‘ጌታን ስላዘለ’ ከሆነ አክብሮቲ
አስተዋሽ ቅርፃቅርፅ ቢሆን እንጂ እንጨቱ
መስቀሉ ከጠፋ ሺ ስንት አመታቱ?!
እንዲያ ከሆነማ ሂሳቡ ቀመሩ
ለመስገድ አትቦዝን ለየመቃብሩ
ያስታውሳልና ነገረ ስርኣቱ
ጌታህ ካፈር በታች ለነበረበቱ::
የመሲህ ባሪያ ሆይ ንቃ ተረጋጋ
ይሄ ነው እውነታው ካልፋ እስከ ኦሜጋ፡፡
ግጥሙ “አዑባደል መሲሒ ለና ሱኣሉን” የሚለው የኢብኑ ቀይም አልጀውዚያህ ረሒመሁላህ ድንቅ ግጥም ግርድፍ ትርጉም ነው፡፡ [ኢጋሠቱል አልለህፋን፡ 2/290]
https://t.me/amhakfelagijemaa
130 viewsحيدر مزمل, 04:08