2022-08-10 11:44:56
በጣም አስቸኳይ የበረከት ስራከወንድሜ ዓምደ ብርሃን ቻናል የተወሰደ...ይነበብ!
የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ወዳጆች የሆናችሁ ይህ በረከት እንዳያመልጠን... የ5 ብር ካርድ ከ5 ደቂቃ በላይ አያዋራም ለጊዮርጊስ የምናወጣት 5 ብር ግን እስከ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ድረስ ታነጋግረናለች ምህረት እና ይቅርታን ታስገኝልናለች....
ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ
ይህችን መልእክት የምታነቡ ሁላችሁም የበኩላችሁን ተባበሩኝ መልእክቱ የኔ ሳይሆን የሊቀ ሰማእታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ነው ...
ወደ ጉዳያችን ልግባና በቡሬ ወረዳ ሽማጎ በተባለች ትንሽየ ሰፈር ውስጥ የሰማእቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በሚገርም ሁኔታ ተጠናቆ ...ግን አንዳንድ ያልተሟሉ ነገሮች አሉ።
ለምሳሌ ብነግራችሁ 2 ካህናት እና 3 ዲያቆናት ብቻ ናቸው ያሉት... እነዚህም ያለምንም ክፍያ ነው የሚያገለግሉት። በዚያ ላይ ደግሞ የክብረ በዓል ጊዜ ሊቃውንቱ ማኅሌቱን ሲቆሙ ጸናጽል የለም። መቋሚያ የለም። ...እነዚህ እና መሰል ችግሮች ስላሉ የእኛን ኪስ ይመለከታሉ። አስቡት እኛ አቅም ላይኖረን ይችላል። ግን እመኑኝ ይህንን መልእክት ሼር በማድረግ ብትተባበሩኝ ግን ልዑል እግዚአብሔር መፍትሄ አያሳጣንም። እኛም ደግሞ ከ5 ሳንቲም ጀምሮ እስከ ≥10 ብር ለእግዚአብሔር ዓሥራት በኩራት ብናወጣ ምን ያክል ጽድቅ ይሆንልን??
እውነት እላችኋለው ሰው በሌለበት ሰው ሆኖ መገኘት እንዴት አይነት መመረጥ መሰላችሁ?? እርግጠኛ ነኝ ሁሉን የሚያውቅ እግዚአብሔር ነው። ያላችሁ በብራችሁ የሌላችሁ በጸሎታችሁ እና ሼር በማድረግ ታሪክ እንስራ! ብናውቀው ኖሮ የእግዚአብሔርን ቤት ለመስራትም ሆነ ለመርዳትም እኮ መመረጥ ያስፈልጋል። አስታውሱ የኢየሩሳሌምን ቤተ መቅደስ ሊሰራ የፈለገው ዳዊት ነበር። ግን አልተፈቀደለትም። ለሰሎሞን ነበር የተፈቀደለት።
"ስጡ ይሰጣችኋል በምድር ያላበደረ በሰማይ የሚያበድረው የለም ፣ በምድር ርኅራኄ ያላደረገ በሰማይ የሚራራለት አያገኝም ፣ በዚህ ዓለም ማደሪያ ሰጥቶ እንግዳውን ያልተቀበለ በዚያች በፍርድ ቀን የሚያሳድረው አይኖርም ፣ በምድር ንስሐ ካልገባ በሰማይ ንስሐ የለም....(ድርሳነ ሚካኤል ዘመስከረም)
ስንቅ እንያዝ በማይታበል ቃሉ ይምረናልና " "ለዘጸውዓ ስመከ ወለዘገብረ ተዝካረከ ወለሐነጸ ቤትከ እምህር ለከ ፣ ስምህን የጠራውን መታሰቢያህን ያደረገውን ቤተ ክርስቲያንህን ያነጸውን ይቅር እልልሃለው" ...እንግዲህ ለጠቢብ አንዲት ቃል ትበቃዋለች ሰማእቱ 7 ዓመት ተሰቃይቶ ያገኛትን ክብር እግዚአብሔር ስለሚወደን እንኩ ለእናንተም ይለናል....
=> እኔ ያሰብኩት የባንክ አካውንት በሰማእቱ ስም ይከፈት ከዚያ በኋላ ሁሉም ሰው የሚችለውን ያበርክት ምናልባት ይህንን መልእክት አይቶ ሙሉውን የሚሸፍን ሰው እንዳለ ማን ያውቃል? ወይም ሌላ የተሻለ አማራጭ ካለ እንነጋገር "ተናገር ወኢታርምም ተናገር ዝም አትበል"... አደራ በሰማእቱ ስም በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም በኮከበ ፋርስ ስም ብላችሁ እዚህ ላይ አስተያየት አስቀምጡልኝ ምን ማድረግ እንዳለብን እንድንነጋገር እፈልጋለው እንዳያመልጠን ሌሎች እንዳይቀድሙን እንፍጠን!!!
እግዚአብሔር ይመስገን ብዙ ልጆችን እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ለማነጋገር እየሞከርን ነው። የባንክ ሰራተኞች ናቸው። ሁሉም በይሁንታ ተስማምተዋል። ለክርስቲያኖች ዓሥራት በኩራት ማውጣት ግዴታ ነው። ስለዚህ ይህንን ዓሥራት በኩራት በባንክ አካውንት በማስገባት በአንድ አሰባስበን #ለሽማጎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን መላክ ነው። እግዚአብሔር ይመስገን ያሰብነው ከተሳካ ጭራሽ ለካህናቱም ደመ_ወዝ መክፈል እንችላለን! በየወሩ ባንችል እንኳን በየሦስት ወሩ ደመ_ወዝ መክፈል እንችላለን! ስለዚህ ሁላችሁም የመንግስትም ሆነ የግል ሰራተኞች #ዓሥራት በኩራታችንን ለሽማጎ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን " በሚል መሪ ቃል እንረባረብ። አካውንቱን እኔ ራሴ እንዲከፈት አደርጋለሁ! ከሊቀ ካህናት ቀሲስ መሐሪ ጋር ስልክ እንደዋወላለን። እናንተም ከፈለጋችሁ 0933142862 #ዓምደ_ብርሃን ነው ስልካችሁን የሰጠን እያላችሁ ማውራት ትችላላችሁ። ሃሳብ አስተያየት እቀበላለሁ።
• በብር መርዳት ለምትፈልጉ 1000161193888
Agerie Hunegn Shitu
• ከእኔ ጋር ማውራት ለምትፈልጉ
0910990644 ዓምደ_ብርሃን
•የደብሩን አስተዳዳሪ ከፈለጋችሁ
0933142862
0929153524 ቀሲስ መሐሪ
ለተጨማሪ መረጃ፦@AmdE_MeleK_21
#
Share
248 views08:44