Get Mystery Box with random crypto!

የህግ ተማሪዎች ህብረት🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopianlawstudentsunion — የህግ ተማሪዎች ህብረት🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopianlawstudentsunion — የህግ ተማሪዎች ህብረት🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopianlawstudentsunion
ምድቦች: ብድር, ግብሮች እና ህጎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.72K
የሰርጥ መግለጫ

የኢትዮጵያ የህግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ህብረት
Ethiopian law school students Union (ELSSU)
lawschoolstudentsunion@gmail.com

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-22 16:47:09 ህግን ለማወቅ እንዲሁም ህግ ነክ መረጃዎችን ለመከታተል አዳዲስ ህጎችን፣ አዋጆች፣ መመሪያዎች እና ደንቦችን የሚያገኙባቸው ጠቃሚ የቴሌግራም ቻናሎች ናቸው።

የህግ መምህር፣ ጠበቃ፣ ህግ ባለሙያ፣ ነገረ ፈጅ፣ ህግ አዋቂዎች ከፈለጉም በእነዚህ ቻናሎች ያገኛሉ።
ከዚህ በታች እንደምርጫ ከቀረቡት ውስጥ መርጠው ይቀላቀሉ ቤተሰብ ይሁኑ፣ ህግና ስርዓት ይወቁ ምክር ያግኙ።
845 views13:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 16:16:55
የሰ/መዝ/ቁ 175578
~~~
የወንጀል ህግ አንቀፅ 543(3) ድንጋጌ የአሽከርካሪነት ሙያ ማረጋገጫ ፈቃድ ሳይኖራቸው ተሽከርካሪን በማሽከርከር ጉዳት ባደረሱ ሰዎች ላይም ተፈፃሚ ስለመሆኑ
~~~ Click Ethiopian Laws ~~~
987 views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 16:16:55
የሰበር መዝ/ቁ. 230167
========
በፌደራል ፍርድ ቤቶች አዋጅ ቁጥር 1234/2013 መሰረት ተገድዶ የመያዝን ህጋዊነት ለማረጋገጥ የሚቀርብን አቤቱታ ተቀብሎ የማየት የመጀመሪያ ደረጃ የዳኝነት ስልጣን ያለው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስለመሆኑ በፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በቀን ሐምሌ 28 ቀን 2014 የተሰጠ የህግ ትርጉም።
~~~ Click Ethiopian Laws ~~~
955 views13:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 14:30:21 አዲሱ የግል ሠራተኞች የጡረታ አዋጅ ቁ. 1268/2014
New Private Employees' Pension Proclamation No. 1268/2022
1.1K views11:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-23 08:49:57
የፌደራል ፍርድ ቤቶች የችሎት ስርዓት

።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
https://t.me/lawsocieties
4. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 1 እና 2 የተደነገገው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ዳኛ፣ ዓቃብያነ ህግ፣ ጠበቃ አካባው ውስጥ ለወንድ ሙሉ ልብስ (ሱፍ የጨርቅ) ኮትና ሱሪ፣ ሸሚዝ እና ከረባት እንዲሁም ለሴት ሙሉ ልብስ ሱፍ/የጨርቅ) ኮትና ሱሪ ወይም ቀሚስ ፣ ሸሚዝ ወይም ሹራብ መልበስ እና ካባ እስከ አንገት ድረስ በቁልፍ ወይም በዚፕ የተዘጋ መሆን አለበት፡፡

5. ማንኛውም ነገረፈጅ ለወንድ ሙሉ ልብስ ኮትና ሱሪ፣ ሸሚዝ፣ ከረባት እንዲሁም ለሴት ሙሉ ልብስ (ሱፍ ጨርቅ) ኮትና ሱሪ ወይም ቀሚስ፣ ከውስጥ ሸሚዝ ወይም ሹራብ መልበስ አለባቸው፡፡

6. በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ 4 እና 5 የተገለፀው እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ዳኛ፣ የጉባኤ ተሿሚ፣ ዓቃብያነ ህግ፣ በቁም፣ ጅንስ፣ የተቀደደ ልብስ ፣ ቲሸርት፣ የተለያዩ ፅሁፎች ያለባቸውን አልባሳት፣ ሲሊፐር ወይም ሸበጥ ጫማ መልበስ የተከለከለ ነው፡፡

7. ማንኛውም ዳኛ፣ ረዳት ዳኛ፣ ጠበቃ፣ ዐቃቢያነ ህግ ለወንድ በጣም የረዘመ፣ ድሬድ ራስታ ፀጉር ፤ ለሴት እይታን የሚከለክል የፀጉር አሰራር እንዲሁም ኮፍያ - ማድረግ የለበትም የለባትም።

8. የችሎት ፖሊስ ለዚህ ስርዓት የሚውል የደንብ ልብስ እንዲሁም የችሎት አስከባሪ መሆኑን የሚያሳይ መለያ መልበስ አለበት፡፡

መመሪያ ቁጥር 13/2014
ግንቦት 2014 ዓ.ም
የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት
#Share #ሼር #አለ_ህግ #Alehig
@lawsocieties @AleHig
https://t.me/lawsocieties
741 views05:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 08:33:54 Employment law Distance Material Harommaya University , College of Law
776 viewsedited  05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 09:20:57 በጥቅሉ አለምአቀፍ ህግ የሉዓላዊ ሀገራት ግንኙነት የሚመራበትን የህግ ማእቀፍ የሚደነግግ ህግ ሲሆን ተፈጻሚነቱም እንደ ህጉ ባህሪ በፈራሚ ሀገራት፣ በአባል ሀገራት፣ እና እያንዳንዱ ሀገራት ላይ ነው፡፡ ሀገራችንም ከዚህ አንጻር ያላት አለምአቀፍ ግንኙነት በዚሁ ህግ አግባብ የሚመራ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
በዮሃንስ ግርማ
ከንቃተ ህግ፣ ትምህርት እና ስልጠና ዳ/ት
እናመሰግናለን!

#Share #ሼር #አለ_ህግ #lawsocieties #AleHig
https://t.me/lawsocieties
1.1K views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 09:20:57 ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ይቀርባል፡፡ የሚኒስትሮች ምክር ቤትም ስምምነቱ እዲጸድቅ ሲወስን ከላይ የተገለጹ ስምምነቱ እና ማብራሪያው እንዲሁም ረቂቁን ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማቅረብ አለበት፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 11 መሰረት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤትም ስምምነቱን ከተቀበለው የማጽደቂያ አዋጅ ያወጣል።

ሀገራት በአንድ ስምምነት ላይ የተወሰኑ ክፍሎች ላይ ተዓቅቦ (reservation) ማድረግ የሚችሉ ሲሆን በማፅደቅ ሂደቱ ይህ ካለ ማጽደቂያው ይሄንኑ ማካተት አለበት፡፡ በዚህ ሂደት ያለፈ አለምአቀፍ ስምምነት የሀገራችን ህግ አካል ይሆናል፡፡

ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግ ምንድን ነው?
ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግጋት የሚባሉት ከመደበኛው እና ከተፃፈው ስምምነት ወይም ቃልኪዳኖች የሚመነጩ ሳይሆን ከሀገራት አለምአቀፍ ተግባርና ልማድ የሚመነጩ ህግጋት ሆነው ሀገራት በተደጋጋሚነት እና በተከታታይነት ሲተገብሯቸው የቆዩ ጠቅላላ ተግባራዊ ልምዶች (general state practices) እና ሀገራቱ እነዚህኑ እየተገበሯቸው ያሉት ልምዶች እንደ አስገዳጅ ህግ ተቀብለዋቸው (opinio juris) ከሆነ እንደ ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግ የሚወሰዱ ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት በሀገራት አለምአቀፍ ግንኙነት ውስጥ አንድን ግዴታ ወይም መብትን በመቀበል በተደጋጋሚ ተመሳሳይ አቋምና ተግባር ካለ ወደፊት በዚህ ጉዳይ የዚህ ሀገር መብት ወይም ግዴታ ምንድነው ሲባል ይህው ልማድ እንደሆነ ይወሰዳል ማለት ነው፡፡ ይህ የሀገር አቋምና ተግባር በሀገር መሪ፣ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ በሚመለከተው ሚኒስተር፣ አምባሳደር ንግግርና ተግባር ወይም ከሀገሪቱ ተቋማት ወይም ፍርድ ቤት ሊወሰድ ይችላል፡፡ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሀገራትን ወክለው በአለምአቀፍ መድረክ በወከላቸው ሀገር ስም የሚያደርጓቸው ንግግሮች፣ የሚይዝዋቸው አቋሞች ተደጋግመው እና እንደ አለምአቀፍ ግዴታ ሲወሰዱ ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግ ሆነው ወደፊት በሚነሱ መሰል ጉዳዮች ላይም አስገዳጅ ተፈታሚነት ይኖራቸዋል፡፡ ለምሳሌ ድንበር ተሻጋሪ ወንዞችን (ዓባይ) በፍትሀዊነት መጠቀም እና ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያለን አለማቀፍ ድንበር ውዝግብ በተመለከተ ሀገራችን በተወካዮች በኩል በአለምአቀፍ መድረክ የምትይዘው አቋም እንደ ልማዳዊ ህግ እያደገ ስለሚሄድ የሀገሪቱን ዘላቂ ጥቅም ያስጠበቀ ወጥነት ያለው እና የማይናወጽ አቋም ይዞ ጉዳዩን መከታተል ያስፈልጋል፡፡

በስምምነት ህግ ከተጻፉ ጉዳዮች የተወሰኑ ጉዳዮች በአለምአቀፍ ደረጃ ሙሉ ስምምነት በሚያስብል ደረጃ ስምምነት የተደረሰባቸው እንደ አስገዳጅ ህግ ሀገራት በራሳቸው ፍላጎት የሚተገብሯቸው ሲሆን እነዚህ ጉዳዮች የሚታዩበት አግባብ ከፍ ወደሚል ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግነት አድጓል፡፡ ለምሳሌ በተባበሩት መንግስታት ስምምነቶች በክልከላነት የተደነገጉ ሰውን ማሰቃየት፣ እንደ ሰው እውቅና አለመስጠት እና በባርነት አለመያዝ፣ ያለፍርድ ቤት ውሳኔ አለመገደል፣ በአራቱ የጄኔቫ ስምምነቶች የተደነገጉ የጦርነት ወይም የሰብአዊነት ህግጋት ውስጥ የተካተቱ ልዩ ልዩ ጉዳዮች ወደ ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግነት ደረጃ ያደጉ ልምዶች (አለምአቀፍ ግዴታዎች) ተደርገው ይወሰዳሉ (jus cogens)፡፡ እነዚህ ጉዳዮች የእኛም ሀገር ህግ አካል ሲሆኑ በኢ.ፌ.ድ.ሪ. ህገመንግስት፣ የወንጀል ህግ እና ሌሎች ህግጋቶቻችን ውስጥ በስፋት የተደነገጉ ጉዳዮች ናቸው፡፡

ስለ ጠቅላላ የህግ መርሆች
ጠቅላላ የህግ መርሆች የሚባሉት በዲሞክራሲ ስርአት ውስጥ በሂደት የዳበሩ እና በየሀገራቱ የህግ ስርአት ተግባራዊ የሚደረጉ ሆነው በዚህም አለምአቀፍ ተቀባይነት ያገኙ መርሆች ናቸው፡፡ እነዚህ መርሆች በአለምአቀፍ ግንኙነት እና ክርክር አፈታት ሂደት ላይ ተግባራዊ ሊደረጉ የሚችሉ የህግ መርሆች ናቸው፡፡ ለምሳሌ ውል የገባ በውሉ የተጣለበትን ግዴታ እንዲያከብር “ቃሉ ማሰሪያው ነው” (Pacta sunt servanda)፣ በአገራት ግንኙነት ሂደት የቅን ልቦናን መርህ (good faith) መከተል የሚሉ እና መሰል መርሆች ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ መርሆቹ በአንድ ሀገር ብቻ ሳይሆን ስፋት ባለው መልኩ በተለያዩ ሀገራት የህግ ስርአት የዳበሩ መርሆዎች መሆን አለባቸው፡፡

የትኞቹ የፍርድ ቤት ውሳኔዎች ናቸው በአለምአቀፍ ህግ ምንጭነት የሚወሰዱት?
በአለምአቀፍ ህግ የፍርድ ቤቶች ውሳኔ አዲስ ለሚታዩ ጉዳዮች እንደ መርህ መጠቀም የማይፈቀድ መሆኑን ከአለምአቀፍ የፍትህ ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ ስምምነት (ICJ statute) አንቀጽ 59 መረዳት ይቻላል፡፡ በዚሁ ስምምነት መሰረት የውሳኔው ተፈጻሚነት በተከራካሪ ወጎኖች ላይ ብቻ መሆኑን ደንግጓል፡፡ ነገር ግን ከአለምአቀፍ የፍትህ ፍርድ ቤት (ICJ) እና ሌሎች አለምአቀፍ ፍርድ ቤቶች ተፈጻሚነት ያለውን አለምአቀፍ ህግ ለመለየት የራሳቸውን ያለፈ ውሳኔ ተመልሰው የሚያዩበት አሰራር ያለ በመሆኑ አለምአቀፍ ህግ ምንጭነት የፍርድ ቤት ውሳኔን ማግለል የሚቻል አይደለም፡፡ በተለይም ከዚህ ቀደም በተሰጠ ውሳኔ የአንድ አለምአቀፍ ስምምነት ወይም የአንድ ግዴታ መኖር አለመኖር በምን መልኩ እንደተተረጎመ በማጣቀስ የአለምአቀፍ ህግን ለመለየት ጥቅም ላይ ይውላል፡፡ የየትኛው ፍርድ ቤት? የአለምአቀፉ ወይስ ሀገራዊ ፍርድ ቤት ውሳኔ? ለሚለው ጥያቄ ሁለቱም አስፈላጊ ናቸው፡፡ አለምአቀፉ ፍርድ ቤት ከላይ ባነሳነው መልኩ የሚተገበር ሲሆን ሀገራዊ ፍርድ ቤት ውሳኔም ሀገራት አንድን አለምአቀፍ ግዴታ የሚጥልን ጉዳይ ከዚህ በፊት የወሰኑበትን አግባብ በማየት ግዴታው በሀገራቱ የህግ ስርአት ያለ መሆን አለመሆኑን ለማረጋገጥ ወይም ሀገራቱ ጉዳዩን ልማዳዊ አለምአቀፍ ህግ ማድረጋቸውን ለማረጋገጥ በአስረጅነት ጥቅም ላይ ሊውል ይችላል። በዚህ አግባብ ውሳኔዎች የአለምአቀፍ ህግ ምንጭ ይሆናሉ ማለት ነው፡፡

በአለማቀፍ ህግ የታወቁ ምሁራን ከሚያሳትሙት ጽሁፍ የሚገኙ አስተምህሮቶች እና ሌሎች በህጉ በግልፅ ያልተገለጹ ጉዳዮች ላይ ያሉ ትርጓሜዎችና ትንታኔዎች በማስረጃነት የሚታዩ መሰል ጉዳዮች እንደ ሁኔታው የሚያስፈልጉ እና በሁለተኛ ደረጃ በአለምአቀፍ ህግ ምንጭነት የሚገለጹ ናቸው።

የአለምአቀፍ ህግን ተፈጻሚነት ወሰን ያውቁ ኖሯል?
ዓለምአቀፍ ህግ እንደ የህጉ ምንጭ የአፈጻጸሙ ወሰንም የሚወሰን ነው፡፡ ከስምምነት የሚመነጭ አለምአቀፍ ህግ ተፈጻሚነቱ በፈራሚ ሀገራት ላይ ብቻ ሲሆን ፈርመውም በተወሰኑ ጉዳዮች ላይ ተዓቅቦ ያሰሙ ፈራሚ ሀገራት በታቀቡበት ጉዳይ ላይ እንዲፈጸምባቸው አይገደዱም። ከልማዳዊ አለምአቀፍ ህግ ጋር በተገናኘም ከላይ እንዳነሳነው የተፈጻሚነት ወሰኑ የሚታወቀው የሀገራትን ጠቅላላ ልምድ እና እንደ ህግ ግዴታ ጉዳዩን መቀበላቸው ነው። በእያንዳንዱ ጉዳይ ከሀገር ሀገር ይለያያል፡፡ ነገር ግን ቀደም ሲል እንዳነሳነው አንዳንድ አለምአቀፍ ግዴታዎች ጠቅላላ ግንዛቤ ተፈጥሮ በሁሉም ሀገራት እንደ ግዴታ የሚፈጸሙበት ሁኔታ በልማድ ሂደት ስለተፈጠረ እንደነዚህ አይነቶቹ አለምአቀፍ ግዴታዎች የተፈጻሚነታቸውን ወሰን በአለምአቀፍ ደረጃ ያደርገዋል፡፡
851 views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 09:20:57 ስለ ዓለምአቀፍ ህግ ምን ያህል ያውቃሉ?

በዓለም ላይ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት 193 አባላት እና 2 አባል ያልሆኑ ሀገራት በድምሩ 195 የሚሆኑ ሀገራት ያሉ ሲሆን እነዚህ ሀገራት የውስጥ ጉዳያቸውን የሚያስተዳድሩበት ሀገራዊ ህግ አላቸው። ነገር ግን የአንድ አገር ጉዳይ በአገር ውስጥ ጥረት ብቻ ሊሟላ አይችልም፡፡ ስለዚህ ሁሉም አገራት በሚያገናኟቸው ጉዳዮች ላይ በትብብር ይሰራሉ። በተለይም በዚህ ሉላዊነት በነገሰበት ዓለም ሀገራት በፈጠሩት ትስስር ወደ መንደርነት መጥተዋል፡፡ ለትስስሩ ውጤታማነት ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሁነኛ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። ይህ ትስስር የትኛውንም በጎም ሆነ መጥፎ ነገር በቀላሉ ከአንዱ የዓለም ጫፍ ወደ ሌላው ጫፍ እንዲስፋፋ አድርል፡፡ ከወንጀል መከላከል አንጻር ብናየው ወንጀለኞች የወንጀል ሀሳባቸውን በአንዱ አገር አስበው በሌላ አገራት በአካል መገኘት ሳያስፈልጋቸው እንዲፈጽሙ አስችሎአቸዋል፡፡
ከዚህ አንጻር ድምበር ተሻጋሪ ወንጀሎችን መከላከሉም አለማቀፍ ትብብር የሚጠይቅ ጉዳይ መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህ አገራት በየትኛውም ጉዳይ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ግንኙነት ለማድረግ ይገደዳሉ፡፡ ከህግ አሰራር አንጻር ብዙ የጋራ ጥረት እና ትብብር የሚጠይቁ ጉዳዮች አሉ፡፡ አለምአቀፍ ህግ ሀገራት እርስ በርስ የሚኖራቸውን ይሄንኑ ግንኙነት የሚገዛ ህግ ነው፡፡ በአለምአቀፍ ህግ ዋና ተገዚዎች ሀገራት ሲሆኑ፣ እንደየሁኔታው አለምአቀፍ ድርጅቶች እና ግልሰቦችም በዚሁ ህግ የሚመሩበት ሁኔታ አለ፡፡

የዓለም አቀፍ ህግ ምንጮች
በአለምአቀፉ የፍትህ ፍርድ ቤት ማቋቋሚያ ስምምነት (ICJ statute) አንቀጽ 38 መሰረት አለም አቀፍ ህግ የሚመነጨው በዋናነት:-
ከአለምአቀፍ ስምምነቶች፣
 ከአለምአቀፍ ልማዳዊ ህግጋት፣
 ጠቅላላ የህግ መርሆች፣ ሲሆኑ
በተጨማሪም
 የፍርድ ቤት ውሳኔዎች እና
 በአለማቀፍ ህግ የታወቁ ምሁራን ከሚያሳትሙት ጽሁፍ የሚገኝ አስተምህሮት (teachings of the most highly qualified publicists of the various nations) በማስረጃነት የሚታዩ ናቸው፡፡
የአለምአቀፍ ስምምነት (Treaty Laws) ምን እንደሆነ ያውቃሉ?

አለምአቀፍ ስምምነት ሲባል ሁለት እና ከሁለት በላይ የሆኑ ሀገራት እርስ በር ለሚኖራቸው ግንኙነት እንዲመራበት አስበው የሚፈራረሙት የህግ አይነት ነው፡፡ የ1969 የቬና አለምአቀፍ የስምምነት ህግ አንቀጽ 2(1)(ሀ) አለምአቀፍ ስምምነትን ሲገልጸው ‘an international agreement concluded between States in written form….” ሲል ያስቀምጣል፡፡ ትርጉም በመግቢያው ካስቀመጥነው ጋር የሚመሳሰል ሲሆን ይህ ስምምነት የሚፈረምበት የራሱ የሆነ ፎርማሊቲ አለው፡። እርሱም በጽሁፍ መሆን አለበት፡፡ በሀገራችን በአለምአቀፍ ስምምነት መዋዋያ እና ማጽደቂያ አዋጅ ቁጥር 1024/2009 አንቀጽ 2(7) መሰረት አለምአቀፍ ስምምነት ሀገራችን ኢትዮጵያ ከሌላ ሀገር ጋር ወይም ከሌሎች ሀገራት ጋር ወይም ከአለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር የምትፈራረመው ስምምነት እንደሆነ ደንግጓል፡፡ ይህ ትርጉም ከቬናው ስምምነት ትርጉም ጋር ተቀራራቢ ሲሆን አለምአቀፍ ድርጅቶች ጋር የሚደረገውንም ስምምነት አካቶ ይገኛል፡፡ የቬናው ስምምነት ተፈፃሚነት ወሰን በሀገራት መካከል የሚደረጉ ስምምነቶች ላይ ብቻ ነው፡፡ ነገር ግን ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በሀገራት መካከል ከሚደረጉ ስምምነቶች በተጨማሪ ዓለምአቀፍ ድርጅቶች የሚያደርጓቸውን ስምምነቶችንም የሚያካትት መሆኑ ነው፡፡ አለምአቀፍ የስምምነት ህግ ሌሎች አለምአቀፍ ህግጋትን በመከተል መፈረም ያለበት ሲሆን በተለያዩ መጠሪያዎች በተለዋዋጭነት ይጠራል፡፡ እነሱም ስምምነት (agreements)፣ ቃልኪዳን (conventions)፣ ፕሮቶኮል (protocols) ወይም ኮቬናንት (covenants) እየተባለ ሊጠራ ይችላል፡፡ ስምምነቱ አለምአቀፍ ህግ የሚሆነው ተፈራራሚ ሀገራት ሉአላዊ ሀገራት ከሆኑ ብቻ ነው። ይህ ማለት በአንድ ሀገር ውስጥ ያሉ ክልሎች ወይም የአካባቢዎች አስተዳደር አካላት አለምአቀፍ የስምምነት ውል ሊዋዋሉ አይችሉም ማለት ነው። አንድ ሉዓላዊ አገር ከሌላ ሉዓላዊ አገር የክልል አስተዳደር ጋር ስምምነት ማድረግም በአለምአቀፍ ህግ መሰረት ህጋዊ ውጤት የማይኖረው ነው፡፡ ዓለምአቀፍ ስምምነቶች በተለያዩ መስፈርቶች የተለያዩ ክፍፍሎች ቢኖራቸውም ከአባል ሀገራት ብዛት አንፃር በሁለት የሚከፈሉ ሲሆን እነርሱም ባለሁለት ወገን ስምምነቶች (bilateral treaty) እና ባለብዙ ወገን ስምምነቶች (Multilateral treaty) ተብለው ሊከፈሉ ይችላል፡፡ ትርጉሙም ከቃሉ መረዳት እንደሚቻለው የፈራሚ አገራትን ብዛት መሰረት ያደረገ ሲሆን ሁለት ሀገራት ብቻ እርስ በርስ የሚያድጉት ስምምነት ባለሁለት ወገን ስምምነት ይባላል፡፡ የፈራሚ አገራት ብዛት ከሁለት በላይ ከሆነ ባለብዙ ወገን ስምምነት ይባላል፡፡ ለምሳሌ ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገር ሱዳን ጋር ወንጀለኞችን አሳልፎ ለመስጠት የምታደርገው ስምምነት ባለ ሁለት ወገን ስምምነት ሲባል የኢጋድ አባል ሀገራት ፍርደኛን ለማስተላለፍ የሚያደርጉት የጋራ ስምምነት ባለብዙ ወገን ስምምነት ይባላል፡፡ ምክንያቱም የኢጋድ አባል ሀገራት ከሁለት የበለጡ ስለሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህግ ማእቀፍን፣ የአፍሪካ ህብረት እና ሌሎች አህጉራዊ ወይም ቀጠናዊ ባለብዙ ወገን ስምምነቶችን በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ሀገራችን የምትፈርማቸው አለምአቀፍ ስምምነቶች የሚ ጸድቅባቸውን ሂደት ያውቃሉ?
በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ህገ-መንግስት አንቀጽ 9 ንኡስ አንቀጽ 4 እና አንቀጽ 55 ንኡስ አንቀጽ 12 መሰረት አንድ አለምአቀፍ ስምምነት የሀገራችን ህግ አካል እንዲሆን መጽደቅ እንዳለበት ይደንግጋል፡፡ ይህንኑ የህገመንግስቱን ድንጋጌ ለማስፈጸም የወጣው የአለምአቀፍ ስምምነቶች መዋዋያ እና ማጽደቂያ አዋጅ ቁጥር 1024/2009 አንቀጽ 6(1) መሰረት አለምአቀፍ ስምምነትን የመደራደር እና የመዋዋል ስልጣን የጠቅላይ ሚኒስትሩ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ እንደሆነ ደንግጓል፡፡ በዚሁ አንቀጽ ንኡስ አንቀጽ 2 መሰረት ሌሎች የመንግስት ባለስልጣናት መሰል ስምምነቶችን መደራደር እና መዋዋል የሚችሉት ባለሙሉ ስልጣን ውክልና ከተሰጣቸው ብቻ ነው፡፡ በአዋጁ አንቀጽ 4 መሰረት የድርድር ሀሳቡን የሚያቀርበው የመንግስት አካል ባለድርሻ አካላትን በማማከር አስተያየታቸውን ማካተት እና ስምምነቱ አገራችን ላይ የሚጥላቸውን ግዴታዎች ብሎም የሚያስገኘውን ጥቅም በተመለከተ ማብራሪያ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ጽ/ቤት ማቅረብ አለበት፡፡ በዚሁ ህግ መሰረት ስምምነቱ አዲስ ህግ እንዲወጣ እና ነባር ህግ እንዲሻር የሚያደርግ ከሆነ የኢ.ፌ.ድ.ሪ. ፍትህ ሚኒስቴር አስተያየት መጠየቅ አለበት፡፡ አለምአቀፍ ስምምነቱ ከድርድር እና መዋዋል በኋላ በህገመንግስቱ መሰረት በሚኒስትሮች ምክር ቤት እና በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቅ እንዲችል የግድ መቅረብ አለበት፡፡ ለዚህም በአዋጅ ቁጥር 1024/09 አንቀጽ 10 መሰረት ድርድሩን ያደረገው የመንግስት አካል የስምምነቱን ቅጅ፣ የይዘቱን ማብራሪያ አጭር መግለጫ እና ማጽደቂያ ረቂቅ አዋጅ በማዘጋጀት በጠቅላይ ዓቃቤ ህግ ማkkሚያ አዋጅ ቁጥር 943/2008 አንቀጽ 6 ንኡስ አንቀጽ 5(ሐ) መሰረት ከፍትሕ ሚኒስቴር የህግ አስተያየት ተሰጥቶበት
713 views06:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ