የነዳጅ ዋጋ ላይ ጭማሪ ተደረገ።
በአዲስ አበባ ከተማ በነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ላይ ማስተካከያ መደረጉን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የዋጋ ማስተካከያው ከሚያዝያ 24 ቀን 2015 ሌሊት 6 ሰዓት ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን 2015 ዓ.ም የሚቆይ መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
በዚሁ መሠረት፡ -
- ቤንዚን በሊትር 69 ብር ከ43 ሳንቲም ብር
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 71 ብር ከ08 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 71 ብር ከ08 ሳንቲም
- የአውሮፕላን ነዳጅ በሊትር 66 ብር ከ60 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 57 ብር ከ84 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 56 ብር ከ50 ሳንቲም ተደርጓል።
መረጃው የንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር / ኤፍቢሲ ነው።
Via - Tikvah
@EthiopianBusinessDaily