Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopia buna sport clubʳ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiabuna12t — Ethiopia buna sport clubʳ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiopiabuna12t — Ethiopia buna sport clubʳ
የሰርጥ አድራሻ: @ethiopiabuna12t
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 217
የሰርጥ መግለጫ

📩ሀሳብ ወይም አስተያየት ካሎት
በዚህ 👉 @kalabhailuorthማድረስ ይችላሉ
Channel :- @ethiopiabuna12t
Group :- @ethiopiabunasportteam
For cross :- @kalabhailu

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-06-11 13:41:57 በአዲስ መልክ ስለቡና መዘገብ ጀምረናል ቡናማዎቹ

@ethiopiabuna12t
@ethiopiabunasportteam


93 viewsKaleab የየካው, edited  10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-18 07:01:23
የቤቲካን የኢትዮጵያ ቡና ኮከብ ይምረጡ!
በአዳማ ከተማ ከተደረጉ የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች የቤቲካ ምርጥ የቡና ኮከብ ተጨዋች ማን ነው?
እስከ ግንቦት 16 ቀን 2014 ዓ.ም ድምፅዎን ይስጡ! ለሽልማቱ የስልክ ቁጥርዎን BV የሚለውን ኮድ በማስቀደም በ0975898989 እና በ0960898989 በቴሌግራም ቴክስት ያድርጉ ! የቤቲካን ኮከብ ይምረጡ! የ5ዐ ብር ቦነስ ይሸለሙ! ዕጩዎች
Final Results
64%
1. ሮቤል ተክለሚካኤል
4%
2. በረከት አማረ
26%
3. አቡበከር ናስር
4%
4. አማኑኤል ዮሐንስ
3%
5. አሥራት ቱንጆ
17.2K voters135 viewsKaleab የየካው, 04:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-22 21:26:12 https://t.me/Nnewandoldmusic

@ethiopiabuna12t
@ethiopiabunasportteam


174 viewsKaleab የየካው, edited  18:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-21 21:35:57
ዘፈኖችን በ kb size በአነስተኛ መጠን የሚቀርብ ቻናል

ቆየት ያሉ ተወዳጅ ዘፈኖችን
አዲስ የወጡ አልበሞች እና
ዘፈኖችን
ምርጥ የዘፈን ስብስቦችን

እነዚህን ሁሉ በ kb SIZE ለማግኘት joun

@nnewandoldmusic
@nnewandoldmusic
@nnewandoldmusic
140 viewsKaleab የየካው, 18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 20:17:25 https://vm.tiktok.com/ZML4YKupx/
155 viewsTeme, 17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-12 19:45:43
CODE - 23

USER NAME - @Kalabhailu

መልካም እድል

ፎቶ ለመላክ @Habta77 እና @dagiredevil
128 viewsKaleab የየካው, 16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 07:39:29
#የደጋፊ_ማህበር_ምርጫ_ሚያዝያ_2_ነገ_4:00 ሰዓት ይካሄዳል
ክለባችን ኢትዮጵያ ቡና ካሳተመው ማሊያ ውጭ ማንም ሌላ ማሊያ ለብሶ መምጣት አይችልም
12 ለባሹ የሆነ ደጋፊ ሁሉም መምጣት አለበት ምክንያቱም ምርጫው ተዓማኒ እንዲሆን የሁላችንም ተሳትፎ ያስፈልገዋል
የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ማህበር የጠቅላላ ጉባኤ ቀን ነገ ከጠዋቱ 4:00 ሜክሲኮ በሚገኘው የመብራት ሀይል አዳራሽ ጉባዔው የስራ አስፈፃሚ ምርጫ የሚደረግ በመሆኑን እንገልፃለን!
#12_ለባሹ_የሆነ_እንዳይቀር
#የደጋፊ_ማህበር_ምርጫ_ሚያዝያ_2
#ሼርያድርጉትደጋፊዎቻችንጋርእንዲደርስ

@ethiopiabuna12t
@ethiopiabunasportteam


153 viewsKᴀʟᴇᴀʙ የየካው, edited  04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-04 22:13:18 #ዛሬ_15ሺ ላንገባነው? Online ያላችሁ 35 ኦርቶዶክሳውያን ፈልጉ እና 15ሺ እንሙላው!!


https://t.me/BetMetsahfte

https://t.me/BetMetsahfte

https://t.me/BetMetsahfte
130 viewsKᴀʟᴇᴀʙ የየካው, 19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-04 22:12:46 ቅድመ ዳሰሳ | ኢትዮጵያ ቡና ከ ቅዱስ ጊዮርጊስ
April 4, 2022 by ሚካኤል ለገሠ
በደረጃ ሰንጠረዡ አካፋይ እና አናት ላይ ሆነው ነገ የሚገናኙት ኢትዮጵያ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ጠንካራ ፉክክር የሚታይበት ፍልሚያ እንደሚያደርጉ ብዙዎች ይጠብቃሉ። ያለፉትን አራት ጨዋታዎች አንድም ድል ያላገኘው ኢትዮጵያ ቡና የራቀውን ድል በማሳካት ወደ አሸናፊነት ለመምጣት እና የደረጃ መሻሻል ለማግኘት ነገ ተግቶ እንደሚጫወት እሙን ነው። የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ በበኩሉ ባለመሸነፍ ግስጋሴው በመቀጠል አውራነቱን ለማጠናከር እና ከበታቾቹ ያለውን የነጥብ ልዩነት እያሰፋ ለመሄድ በጠንካራ እንቅስቃሴ ጨዋታውን እንደሚቀርብ ይታሰባል።
በአሠልጣኝ ካሳዬ አራጌ የሚመሩት ኢትዮጵያ ቡናዎች ከላይ እንደገለፅነው ወቅታዊ ብቃታቸው አስተማማኝ አይደለም። ከሲዳማ ቡና ጋር አቻ በተለያዩበት ጨዋታ የወትሮ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ በመያዝ ቢጫወቱም በመጨረሻው የማጥቃት ሲሶ ያላቸው ተፅዕኖ ፈጣሪነት እጅግ የወረደ ነበር። ባለፉት ዘጠኝ ጨዋታዎች ከአንድ ጎል በላይ አንድ ጊዜ ብቻ ያስቆጠረው ቡድኑ ጎል ፊት ዓይናፋር እየሆነ መጥቷል። በጠቀስነው የሲዳማ ጨዋታ ጥቃታቸው በግቡ ትይዩ (ዘጠኝ ቁጥር ቦታ) ኳስ የሚቀበል እና አደገኛ ዕድሎችን የሚፈጥር ስል ሰው አለመኖሩን ተከትሎ በግራው በኩል ብቻ የግብ ምንጫቸውን እንዲያደርጉ እና ተገማች እንዲሆኑ አድርጎት ነበር።
በተቃራኒ የቀኝ መስመር በኩል ደግሞ አጥቂው (አቤል) ወደ መሐል ስለሚገባ የቀኝ ተከላካዩ (ኃይሌ) ወደፊት ሲሄድ ቦታውን መሐሪ ለመጠቀም እየጣረ ከጥቅሙ ጉዳቱ ሲያዘነብል ታይቷል። የቡድኑ አዳኝ እና ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ አቡበከር ናስር ግን የተለመደ ተዐምራዊ እግሮቹን ተጠቅሞ በጨዋታው ያላቸውን ቆይታ አርዝሞ ነበር። ተጫዋቹ በነገው ጨዋታም ለጊዮርጊስ ተከላካዮች ተቀዳሚ የትኩረት ማዕከል መሆኑን ሳንጠራጠር መግለፅ እንችላለን። አቡበከር በዘጠኝ ቁጥርም ሆነ በመስመር ሚና ወደሜዳ ቢገባ ራሱ የሚፈጥራቸው አጋጣሚዎች እንዲሁም ለአጋሮቹ የሚያመቻቻቸው ቦታዎች ከፍተኛ ዋጋ አላቸው።
አንድም ጨዋታ እስካሁን ያልተረታው ቅዱስ ጊዮርጊስ በበኩሉ ከኢትዮጵያ ቡና በተቃራኒ በምርጥ ብቃቱ ላይ ያለ ቡድን ነው። ለማሳያም ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጨዋታዎች ሦስት ጎል እያስቆጠረ ሦስት ነጥብ ሸምቷል። በሰበታው ጨዋታም በተሻለ የኳስ ቁጥጥር አስር ጊዜ የተጋጣሚን መረብ ለማግኘት ሞክሮ አምስቱን ዒላማቸውን አስጠብቆ እንደገለፅነው ሦስቱን ከመረብ አገናኝቷል።
በቅዱስ ጊዮርጊስ እየታየ ያለው ጨዋታን ከፍ ባለ ፍጥነት እና ፍላጎት መጀመር ዋጋ እያስገኘ ያለ ጉዳይ ይመስላል። በመጨረሻው ጨዋታ በሁለቱም አጋማሾች የመጀመሪያ 15 ደቂቃዎች ተደጋጋሚ ዕድሎችን በመፍጠር ከሦስቱ ሁለቱን ግብ አስቆጥሯል። በተወሰነ መልኩ ሰበታ ወደ ራሱ የግብ ክልል አፈግፍጎ በሚጫወትበት ጊዜ በመጠኑ የተቸገረ ቢመስልም ልኬታቸውን የጠበቁ ተከላካይ ሰንጣቂ ኳሶችን በማዘውተር ፍሬታማ ለመሆን ሞክሯል። በተቃራኒው ኳስ ዘለግ ላለ ጊዜ የሚይዝ ቡድን ሲገጥመው ግን በቀጥተኛ እንዲሁም የመልሶ ማጥቃት አጨዋወት በግለሰቦች ብቃትም ሆነ በቡድናዊ መዋቅር የተሟላ ይዟታ ያለው ይመስላል። ከዚሁ ከቡድናዊ አጨዋወት ጋር ተያይዞ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪው እስማኤል ኦሮ-አጎሮ ሳይኖር ከሦስት ተጫዋቾች ግብ ማግኘቱ የሚደነቅ ነው። በተለይ ከፊት የተሰለፈው አማኑኤል ገብረሚካኤል ማግባት እንዲሁም ጥቃቶች ላይ መሳተፍ መጀመሩ ለቡድኑ ሁነኛ አማራጭ መሆኑን በአንድ ጨዋታም ቢሆን ተመስክሯል።
በከፍተኛ የደጋፊዎች ድባብ እንደሚደረግ የሚጠበቀው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና የኳስ ቁጥጥር ብልጫ ሊኖረው እንደሚችል ይገመታል። ቅዱስ ጊዮርጊስ በተቃራኒው የቡናን የኳስ ፍሰት በማጨናገፍ ቀጥተኝነት የተሞላበት አጨዋወት ማድረግን ምርጫው እንደሚያደርግ ይታሰባል። ሀይደርን ጨምሮ ለተከላካዮች ሽፋን በመስጠት የተዋጣላቸው አማካዮቹም ተፈላጊዎቹን ኳሶች በመላክ ጥሩ ስለሆኑ የቡና የቤት ሥራ መሆናቸው አይቀሬ ነው። በሰበታው ጨዋታ በግራ መስመር ተከላካይነት የተሰለፈው አዲሱ ተጫዋች ያሬድ ሀሰን ነገም በመጀመሪያ አሰላለፍ ቦታ የሚያገኝ ከሆነ ግን ገና ከቡድኑ ጋር የመዋሀጃ ጊዜ ካለማግኘቱ ጋር ተያይዞ የቡድኑ ስስ ጎን ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ኢትዮጵያ ቡና በቀኝ መስመር በማጥቃቱ ረገድ ደከም ያለ መሆኑ ሲታሰብ ደግሞ ፈረሰኞቹ ብዙም እንዳይጨነቁ ሊያደርግ ይችላል። ቡናማዎቹ በዋናነት መጠንቀቅ ያለባቸው ጉዳይ ደግሞ ለመልሶ ማጣቃት ያላቸውን መጋለጥ በማስተካከሉ ረገድ ነው። ከዚህ ትልቅ ስጋት ውጪ ግን በግል ጨዋታን የመወሰን ብቃት ያላቸው ተጫዋቾች የሚኖራቸው ተሳትፎ ለመሪው ቡድን ትኩረት እንደሚሻ አመላካች ነው።
በጨዋታው የኢትዮጵያ ቡናው ተከላካይ ቴዎድሮስ በቀለ ከጉዳት ሲመለስ አቤል እንዳለ በጉዳት ከነገው ጨዋታ ውጪ ሆኗል። በቅዱስ ጊዮርጊስ በኩል ግብ ጠባቂው ተመስገን ዮሐንስ ፣ እስማኤል ኦሮ አጎሮ እና ቡልቻ ሹራ በጉዳት አሁንም አይኖሩም፡፡
ጨዋታው በኢንተርናሽናል ዳኛ በላይ ታደሰ አማካይነት የሚመራ ሲሆን
ትግል ግዛው እና ሸዋንግዛው ተባባል በረዳትነት አሸብር ሶቦቃ ደግሞ በአራተኛ ዳኝነት ተመድበዋል።
የእርስ በእርስ ግንኙነት
– ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ኢትዮጵያ ቡና በሊጉ 43 ጊዜ ተገናኝተዋል። በእነዚህ ግንኙነቶች ጊዮርጊስ 20 ጊዜ ድል ሲቀናው ቡና ደግሞ 7 ጊዜ አሸንፏል ፤ 16 ጊዜ ደግሞ አቻ ወጥተዋል።
– በ43ቱ የሁለቱ ቡድኖች ግንኙነት በድምሩ 84 ጎሎች መረብ ላይ አርፈዋል። 56ቱን ግብ በማስቆጠር ፈረሰኞቹ ቀዳሚ ሲሆኑ ቡናማዎቹ ደግሞ 28 ኳሶችን ከመረብ አዋህደዋል።
ግምታዊ አሰላለፍ
ኢትዮጵያ ቡና (4-3-3)
አቤል ማሞ
ኃይሌ ገብረተንሳይ – አበበ ጥላሁን – ወንድሜነህ ደረጄ – ስዩም ተስፋዬ
ሮቤል ተክለሚካኤል – አማኑኤል ዮሐንስ – ዊሊያም ሰለሞን
ሚኪያስ መኮንን – አቡበከር ናስር – አስራት ቱንጆ
ቅዱስ ጊዮርጊስ (4-3-3)
ቻርለስ ሉክዋጎ
ሱሌይማን ሀሚድ – ምኞት ደበበ – ፍሪምፖንግ ሜንሱ – ሔኖክ አዱኛ
ያብስራ ተስፋዬ – ጋቶች ፓኖም – ሀይደር ሸረፋ
አቤል ያለው – አማኑኤል ገብረሚካኤል – ቸርነት ጉግሳ
ያጋሩ

@ethiopiabuna12t
@ethiopiabunasportteam


132 viewsKᴀʟᴇᴀʙ የየካው, edited  19:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-29 16:51:14 የ ኢትዮጵያ ቡና የማሊያ ርክክብ !

ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀ እስከ ፐ ከተሰኘ የትጥቅ አምራች ኩባንያ ጋር ዛሬ የትጥቅ ርክክብ ስነ-ስርዓቱን በ ሳፋሪ ሆቴል አከናውኗል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ከ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ላለፉት አምስት አመታት በጋራ የሰራ ሲሆን ኢትዮጵያ ቡና አዲሱን ማሊያ በሁለተኛው ዙር የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ላይ እንደሚጠቀምበት ተገልጿል ።

ኢትዮጵያ ቡና ከ ሀ እስከ ፐ ጋር በጋራ በመሆን አራት ኪሎ አምባሳደር ህንፃ ላይ አዲስ የትጥቅ መሸጫ ሱቅ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚከፍት ገልጿል ።

በትጥቅ መሸጫ ሱቁ ላይ ከክለቡ ማሊያዎች በተጨማሪ የክለቡ አርማን የያዘ የተለያዩ ኮቶች እና ልዩ ልዩ አልባሳት እንደሚሸጡ ተገልጿል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ለ ኢትዮጵያ ቡና ዋናው ቡድን ፣ ከ 20 አመት በታች ፣ ከ 17 አመት በታች እና ለ ሴቶች ቡድን በአጠቃላይ 500 ማሊያ እንደሚያቀርብ ተገልጿል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ለ አሰልጣኞች ከ መቶ በላይ እና ለአሰልጣኝ አባላት 50 የክለቡ አርማን የያዙ ማሊያዎችን እንደሚያቀርብ ተገልጿል ።

በ አጠቃላይ ከ ሀ እስከ ፐ ለ ኢትዮጵያ ቡና ያቀረባቸው ትጥቆች ዋጋ ሶሰት ሚሊየን 25 ሺህ ብር እንደሆነ ተገልጿል ።

ከ ሀ እስከ ፐ ከዚህ ቀደም የሀበሻ ቢራን የብራንድ የትጥቅ መሸጫ ሱቅን የከፈተ እና በዘርፉ ላይ የስምንት አመት ልምድ ያለው ሲሆን በ ኢትዮጵያ ቡና ማሊያ እጅጌ ላይ የድርጅቱ አርማ እንደሚቀመጥ ገልጿል ።

@ethiopiabuna12t
@ethiopiabunasportteam


143 viewsKᴀʟᴇᴀʙ የየካው, edited  13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ