Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤ ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ ሙስሊም ኮሚኒቲ ጋር በዶሐ | "ኡማ ቲቪ " Tv

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤ ልዑካን ቡድን ከኢትዮጵያ ሙስሊም ኮሚኒቲ ጋር በዶሐ ውይይት እያደረገ ነው ።

ግንቦት /3/2015

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ልዑካን በዶሐ ከሚኖሩ የኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ወገኖቹ ጋር ከሚያደርገባቸው ዘረፈብዙ ውይይቶች በተጨማሪ የኮሚኒቱ አባላት ለጠቅላይ ምከር ቤቱ የተለያዩ ጥያቄዎችን አነሰተዋል- ከእነዚህ ውሰጥ
-የኢትዮጲያ መስሊሞች የሃይማኖታቸው መገለጫ በሆነው ሒጃብ ጉዳይ በጉራጌ ክልል በጉንችሬ ከተማ የሚደረገው መገፋት ዘላቂ ወጥነት ባለው መንገድ መፍትሄዉ ምንድን ነው?

-የሙስሊሞቸ ቀልብ ማረፊያ የሆነው እና የአላህ ቤት መስጅዶች ከመቼውም ጊዜ በበለጠ እየፈረሰ በመሆኑ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ተጨባጭ መፍትሄ ማምጣት ለምን ቸገረው?

-በውጪ አገር የምንኖር ሙስሊም ወገኖቻቹህ በማህበራዊ ኑሮቸን ውስጥ 'የኒካህ ሰርተፍኬት' ለማግኘት የቃዲ ችግረ አለብን

-በሰኮላ ሽፕ ዙሪያ ያለባቸውን ችግር አንስተዋል

-በሃይማኖታችን አትለያዩ አንድነት የጥንካሬያችሁ መገለጫ ነው ፤የሙስሊም ጌጡ ህብረቱ ነው የሚል ኢስላማዊ አሰተምህሮት ቢኖርም በየኮሚኒቱ ችግር ሆኖ ቆይቷል ይህ ችግር በዚህ ለውጥ ዘመን ሊለወጥ ይገባል
-በእዚህ የኮሚነቲ ውይይት ላይ የአወሊያ ትምህርት ጉዳይ በስፋት ተነሰቷል

-በኳታር የመጅሊስ ቅርጫፍ አንዲከፈትም ጠይቀዋል
በ ኮሚነቲ ውይይት ላይ በርካታ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን፣ የልዑካን ቡድኑ ምላሽ እንደደረሰን የምንገልፅ ይሆናል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤ ልዑካን ቡድን ከእዚህ የኮሚኒቲ ውይይት በኋላ በቀጠዩ ቀናት ወደ አገር ቤት ይመለሳል ተብሎ ይጠበቃል።