Get Mystery Box with random crypto!

Ethiomewlid ኢትዮ መውሊድ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomewlid — Ethiomewlid ኢትዮ መውሊድ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiomewlid — Ethiomewlid ኢትዮ መውሊድ
የሰርጥ አድራሻ: @ethiomewlid
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.18K
የሰርጥ መግለጫ

ሙሐመድ ﷺ ዉዴታዎ ያሰባስበናል፤ በሙሐመድ ፍቅር አንድ ነን! አንድነታችን በሙሐመድ ፍቅር ነው።
የፌሰቡክ ፔጃችንን ላይክ በማድረግ ይቀላቀሉ፦
Fb.com/Ethiomewlid
የዩትዩብ ቻናላችን Subscribe አድርጉ!
https://goo.gl/ohhc8z
በ ኢኒስታግራም በዚህ ሊንክ Follow ያድርጉ
Instagram.com/ethiomewlid

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-02-21 19:26:43 ኢስራእ እና ሚእራጅ

አሁን ያለንበት ወር የተከበረ በሂጅራ አቆጣጣር ረጀብ ይባላል። ይህ ወር ትልቅ ወር ነዉ፡፡ምንነቱ ነዉ ትልቅ ቀን ያሰኘዉ??ኢንሻ አሏህ ከደርሱ እንማራለን,,,,,

አል- ቁድስ☞ቤተልሔም☞ጡሩ ሲናእ☞ ቁዱሱ (በመካና ሰማይ መኃል)
የኢስራእ መድረሻ(አል-መድነቱ ሙነወራህ፤መከቱል ሙከረማህ)

ኢስራእ እና ሚእራጅ አሏህ ለነቢያችን صلى الله عليه وسلم ላይ ከስጣቸው
ሙዕጂዛዎች(ተኣምራቶች) አንዱ ነው::

ይህም የተከሰተው በረጀብ ወር በ27ኛው ለሊት ነው

قال تعالى {{سبحان الذي أسرى بعبده ليلا من المسجد الحرام إلى المسجد أقصا الذي باركنا حوله لنريه من آياتنا إنه هو السميع البصير}}
አሏህ በተከበረ የቁረአን አንቀፁ ላይ
« ጥራት(ለአሏህ) ይገባው ባሪያውን የለሊት ጉዞ ከመስጊደ አል―ሀራም እስክ መስጊደ አል―አቅሷ እንዲጓዝ ላደረገው ይህ(መስጊደ አል―አቅሷ) ዙሪያው በበረካ የተሞላ እንዲሆን አደረግነው ይህንን ጉዞ እንዲያደርግ የተደረገው ተዐምራት ልናሳየው ዘንድ ነው እሱ(አሏህ) ሰሚና ተመልካች(የሆነ ጌታ) ነው።ይለናል

ኢስራእ ፦ማለት የሌሊት ጉዞ ሲሆን

ሚዕራጅ ፦ማለት ወደ ሰማይ ያረጉበት(የወጡበት) ሁኔታ ነው።

ما القصود من المعراج؟

ሚዕራጅ በማድረጋቸው ምንድን ነበር የተፈለገበት?

ما المقصود من المعراج هو تشريف الرّسولﷺ بإطلاعه على عجائب في العالم العلوي

መልእክተኛው ﷺሚዕራጅ (ወደ ላይኛው ዓለም ማረግን
(መውጣትን))
በማድረጋቸው የተፈለገበት መልእክተኛውንﷺ ማላቅ እና በላይኛው ዓለም ያሉ አስገራሚ ነገራቶችን ማሳየት ነበር።

ከተመለከቷቸው አስደናቂ ነገራቶች መካከል፦
①) በ 7ተኛው ሰማይ በይተ አል―መዕሙርን የተከበረ የሆነውን ቦታ አይተዋል፤ ይህ (በይተ አል―መዕሙር) የምድር ነዋሪዎች(የሰው ልጅ እና አጋንንት)ቂብላቸው ከዐባ እንደሆነው ሁሉ ለሰማይ ነዋሪዎችም(ለመላኢኮች) ቂብላቸው ይህ በይተለ አል―መዕሙር ነው ።

ታዲያ በዚህ በይተል መዕሙር 70,000 (ሰባ ሺህ)መላኢኮች በየቀኑ ይገቡና ይሰግዳሉ ከዛም ይወጣሉ ሰግደው የወጡት ሁለተኛ አይመለሱበትም ነበር
②) አሁንም በ 7 ተኛው ሰማይ ላይ ሲድረተ― አል ሙንተሀን ተመልክተው ነበር።
ይቺ ሲድረተ አል―ሙንተሀ ትልቅ ግዝፈት ያላት ዛፍ ስትሆን አሏህ ከፈጠረው ፍጥረት አንድም ውበቷን ለመግለፅ አይችልም(ቃላት ያጥረዋል)።
ስሪታቸው ከ ወርቅ የሆነ በሆኑ ቢራ ቢሮዎች ያሽቆጠቆጠች ናት ። የዛፋ መሰረት ከ 6 ተኛው ሰማይ ሲነሳ መድረሻዋ 7 ተኛው ሰማይ ነው።

③) በግዝፈት አሏህ ከፈጠራቸው ትልቅ የሆነውን ዐርሺንም ተመልክተዋል

ሌሎችንም ጭምር ...

መልእክተኛውﷺከጅብሪል ዐለይሂ ሰላም ጋር ከሲድረተ አል ―ሙንተሀ ብሀላ ተለያይተው ነበረ።

ከዛም ብቻቸውን የሶሪፈ አል― አቅላምን ድምፅ ሰምተው ነበር የዚህን የሶሪፈ አል ― አቅላም ድምፅን የሰሙት መላኢኮች ከ ለውሀል አል መህፉዝ የተፃፈውን ወደ ራሳቸው መፅሀፍ ሲገለብጡ ነበር።

እዚሁ ቦታ ላይ ሁነው ነበር በፍጡራን ባህሪ የማይገለፅ የሆነውን የአሏህን ንግግር የሰሙት

ከንግግሩም የ50 ሶላቶች ግዴታነትን ተገነዘቡ ።

ይህ ቦታ ከ ሲድረተ አል―ሙንተሀ በላይ ያለ ሲሆን

አንዳንድ ሰዎች እንደሚሉት አላህ ይጠብቀን እና አሏህ የሚገኝበት የመጨረሻ መኖሪያው ላይ ነበር ይላሉ ይህ ግልፅ የሆነ ክህደት ሲሆን ፍጥረታትን የማይመስለው አሏህ ለመኖሩ ቦታና አቅጣጫ አያስፈልገውም።

አንዳንድ ማስጠንቀቂያዎች
ወደ 6ተኛው ሰማይ በተመለሱ ሰዐት ነቢዩ ሏህ ሙሳ ዐለይሂ ሰላም መልእክተኛውን ﷺ ጠይቀው ነበር ጥያቄውም፦
አሏህ በኡመተዎ(በህዝቦቾ)ላይ ስንት ሶላትን ግዴታ አደረገ?
መልእክተኛውም ﷺ
50 ሶላቶችን አሉ።

ነቢዩ ሏህ ሙሳም
*«ارجع وسل ربك التخفيف»*

ማለትም፦ ተመለስ ጌታህንም እንዲቀንስልህ ጠይቅ ማለታቸው

የተፈለገበት አሏህ በቦታ ተገልፆ እሱ ወዳለበት ቦታ ሂድ *ማለት ሳይሆን*

በዚህ አገላለፅ የተፈለገበት *ወህይ ወርዶልህ የሶላት ግዴታነትን የተረዳህበት ወደ ሆነው ቦታ ተመለስ* የሚል ነበር የተፈለገበት

አንዳንድ ሰዎች ከሚናገሩት ንግግር አሁንም ማስጠንቀቅ ይገባናል እሱም፦

«መልእክተኛው ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም እና ጅብሪል የሆነ ቦታ ላይ ሲደርሱ ጅብሪልም አለ ይላሉ«እኔ ከዚህ በላይ ከተጓዝኩኝ ተቃጠልኩኝ ነገር ግን አንተ ከተጓዝክ አለፍክ» ይሄ አባባል ውሸት የሆነና ተቀባይነት የሌለው ነው።

ሌላው መልእክተኛው ﷺ ጅብሪልን ዐለይሂ ሰላም አሏህ በፈጠረው ትክክለኛ ቅርፁ ለ2ተኛ ጊዜ ተመልክተውታል።
①ለመጀመሪያ ጊዜ የተመለከቱት በመካ ውስጥ አጅያድ በተባለች ቦታ ከነ 600 (ስድስት መቶ) ክንፎቹ ሲሆን እያንዳንዱ ክንፎቹ የሰማይን እና የምድርን አድማስ ሸፍኖ ይይዝ ነበር በዚህ ሰአት ነበር ልክረ ሲመለከቱት መልእክተኛው ﷺ ራሳቸውን የሳቱት

② በዚች በተባረከች ለሊትም ለ 2 ተኛ ጊዜ አሏህ በፈጠረው ትክክለኛ ቅርፁ ተመልክተውታል

ይህንን አስመልክቶም አሏህ በተከበረ የቁርአን አንቀፁ ላይ ይለናል
*{وَلَقَدْ رَءاهُ نَزْلَةً أُخْرَىٰ عِنْدَ سِدْرَةِ المُنْتَهَىٰ}*١٤ سورة النجم
ማለትም፦
*«በርግጥ ለ 2 ተኛ ግዜ በሲድረተ አል―ሙንተሀ ላይ ተመልክቶታል»*

ነገር ግን በ2 ተኛ ጊዜ ምልከታቸው እንደ መጀመሪያው ራሳቸውን አልሳቱም ነበር ልቦናቸው ብርታት እና ጥንካሬ ታክሎበት ስለ ነበረ

ጅብሪል ዐለይሂ ሰላም ወደ መልእክተኛው ሶለ አሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ቀርቦም ነበረ በመካከላቸው የሁለት ክንድ እና ከዛም ያነሰ እርቀት እስኪኖራቸው ድረስ

ይህንን በተመለከተ አሏህ እንዲህ ብሎናል
*{ثُمَّ دَنَا فَتَدَلَّىٰ【 ٨】فَكَانَ قَابَ قَوْسَيْنِ أَوْ أَدْنَىٰ【٩】* سورة النجم
ማለትም
ከዛም ቀረበ ያለው ርቀት 2 ክንድ እና ከዛም ያነሰ እስኪሆን ድረስ

የዚህን የቁርአን አንቀፅ ትርጉም በተመለከተ ዓኢሻ ረዲየ አሏሁ ዐንሃ እንደተናገረችው «እኔ ከዚህ ኡማ (ህዝብ) የመጀመሪያው ጠያቂ ነኝ በዚህ አንቀፅ ላይ ማን እንደተፈለገበት »ትላለች።

*فقال " إنما هو جبريل لم أره على صورته التي خلق عليها غير هاتين المرتين"*

መልእክተኛወምﷺበዚህ የተፈለገበትማ ጅብሪል ነበር አሏህ በፈጠረው ቅርፁ ከሁለቱ እይታ ውጭ ሌላ አላየሁትም ነበር ።ብለዋል

በዚህ የቁርአን አንቀፅ አንዳንድ ሰዎች እንደሚቃጥፉት አይደለም የተፈለገበት

ይላሉም በዚህ የቁርአን አንቀፅ አሏህ ነበር የተፈለገበት ይላሉ በነሱ አባባል ሲጠጋ፣ ሲቀርባቸው የነበረው እሱ (አሏህ)ነው ይላሉ በነሱ አባባል ይህ አባባላቸዉ የተሳሳተ መሆኑን ሁላችንም ልናዉቅ ይገባል

አሏህ ከጥመት ይጠብቀንና!
661 views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-21 19:24:54 ✧ ነቢያችን (ሷለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በ
« #ኢስራእ_እና_ሚእራጅ» ጉዞ ላይ ካዩዋቸው አስገራሚ ነገሮች ↶
------------ ★ ------------
ሙጃሂዶችን (ፊ-ሰቢሊላህ/ለ አሏህ ብለው የሚታገሉት)ን ተመለከቱ በሁለት ቀናት ውስጥ በአንደኛው ቀን የዘሩትን በሚቀጥለው ቀን
በሚያጭዱ ሰዎች ምስል አዩዋቸው። ፈጣን በሆነ መልኩ ይዘራሉ፣ ያጨዳሉ። ጂብሪል እነዚህ በአላህ መንገድ «ፊ ሰቢሊላህ» የሚታገሉ ሰዎች ናቸው አሏቸው ። በአላህ መንገድ የሚደረገው ትግል ሁለት አይነት ነው::

➳ አንደኛው በመሳሪያ የሚሆን ጂሃድ ሲሆን
➳ ሁለተኛው ደሞ ማስረጃ በማቅረብ በዒልም የሚሆን ነው ።
➳ ይህ በማስረጃ የሚታገል ሰው ያ በመሳሪያ ጂሃድ ያደርገ ሰው ምንዳ ያክል አለው ።
➳ ዛሬ ባለንበት ጊዜ ጨለማ በበዛበት ጊዜ በጥሩ የሚያዝና በመጥፎ የሚከለክል ሰው፤ በተነሳሽነትና በጥንካሬ፤ በብርታት የሚሰራ ሰው በአላህ መንገድ ላይ የሚታገል ሙጃሂድ የሆነ ሰው ነው።
➳ ሙጃሂዶች በአኺራ ላይ ከፍ ያለ ደረጃ አላቸው ረሱላችን (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ) እንዲህ አሉ፦
➳ [ሱናዬ በሞተበትና በጠፋበት ጊዜ ሱናዬን ህያው የሚያደርገ ሰው የሸሂድ አጅር አለው] ብለዋል [በዚህ ሐዲስ ላይ ሱና የተፈለገበት ሸሪዓ ነው] ረሱላችን የመጡበት መንገድ ማለት
ነው ፣ ማለትም አቂዳቸውን ያሰራጨ ያስተማረ ሰው ይህንን አጅር ያገኛል ።

--ኢስራእ እና ሚዕራጅ ብርሃናዊ ጉዞ---
594 viewsedited  16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-02 19:29:17 ሙሐመድ ነቢዬ
https://vm.tiktok.com/ZSeDVfqbr/
1.0K views16:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-14 10:07:40 #ቲላወህ || ሼይኽ አብዱልሐኪም አሕመድ ሐፊዘሁላህ ..


2.8K views07:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-12-12 10:16:44

3.3K views07:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-23 10:47:02
4.2K views07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-09-23 10:46:58 ወሃቢያዎች እና ለአላህ ‘አስማእ ወ ሲፋት’ን ማፅደቅ በሚል የሚደሰኩሩት የተመረዘ እሳቤ!
•┈┈┈•✿❁✿•┈┈┈•
# ደፍዑ_ሹበሂ_ተሽቢህ (1)
ምስጋና ለተጥራራው ጌታችን አላህ ይሁን። ሰላትና ሰላም በውዱ በሰይዳችን ላይ ይሁን። በመቀጠል፤
አሏህ እንዲህ ብሏል፤
{ ﺍﻟﺮَّﺣْﻤَٰﻦُ ﻋَﻠَﻰ ﺍﻟْﻌَﺮْﺵِ ﺍﺳْﺘَﻮَﻯٰ { ‏[ ﻃﻪ 5 : ]
«አል ረህማን ዓርሽን የተቆጣጠረው ነው» ጣሀ 5
ማንኛውንም ልቡ ያልታወራ ጤናማ ሙስሊም ይህንና ይህን የመሰሉ አንቀፆችን ሲሰማ ቆም ይላል! ,,, አላስፈላጊ እሳቤዎችን ከማሰብ ይቆጠባል። አንቀፁ ለአሏህ የጉድለት እና መመሳል ትርጉም ከማስተላለፍ ፈፅሞ የራቀ መሆኑን ጠንቅቆ ያውቃል።
ነገር ግን ዝንባሌውን በመከተል የተጠመደ አመሳሳይ ከሆነ፤
☞ "ሰማያት አሏህን ተሸክመዋል" ፣
☞ "አላህን ፍጥረታቱ ያካብቡታል"፣
☞ "አላህ ከዓርሽ ፈላጊ ነው" ወይም
☞ "አሏህ ዐርሽ ላይ ተቀምጧል/ ተደላድሏል"
☞ "አርሽ በላይ ከፍ ብሎ ተንሳፏል"
የሚሉ መጥፎ መልዕክቶችን ሊረዳ ይችላል፤ አላህ ማስተዋል የነፈገው ከሆነ።
◆ነገር ግን አሏህ የመራው፦
ኢማሙ ሻፊዒይ እንዳሉት ሁሉ
" ﺃﻣﻨﺖ ﺑﻼ ﺗﺸﺒﻴﻪ ﻭﺻﺪﻗﺖ ﺑﻼ ﺗﻤﺜﻴﻞ .."
"ያለ ምንም ማመሳሰል እን ተሽቢህ አምኜያለው" ሊል ይገባል
እንዲሁም ኢማም አሕመድ እንዳሉት፦
" ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻛﻤﺎ ﺃﺧﺒﺮ ﻻ ﻛﻤﺎ ﻳﺨﻄﺮ ﻟﻠﺒﺸﺮ
"ኢስተዋ አሏህ በጠቀሰው መልኩ እንጂ በሰው ልጅ አይምሮ ከሚሳለው አተረጎገም የፀዳ ነው"
ኢማም አሕመድ ይህን ያሉበት ምክኒያት፡
ይህንን ቃል ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻌﺮﺵ የሚለውን
ለሰው/ ለፍጡር ስንጠቀመው የሚያስረዳው ትርጉም ለአሏህም ያንን ቃል በመጠቀም ስንገልፀው ለፍጡር በምንጠቀመው አገላለፅ ፈፅሞ እንዳንቶረግመው ለማስጠንቀቅ ሲባል ነው።
ለምሳሌ፦
ﻓﻼﻥ ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻌﺮﺵ
"አከሌ አርሽ ላይ ኢስቲእ አደረገ" ቢባል
ኢስተዋ የሚለው ብዙ ትርጉም የያዘ ቢሆንም በቀጥታው የምንረዳው ያ ሰውዬ "ዙፋን ላይ መደላደሉን ነው" !
ልብ ልንለው የሚገባው ግን ይህ አተሮጋገም መደላደልም ሆነ መቀመጥ ለሱ መገለጫ እና ተገቢ ለሆነለት (ለፍጡር) ነው።
በዐረበኛ ቋንቋ ይህንኑ ቃል ለንጉስ ስንጠቀመው ግን,, ከአካላዊ ትርጓሜ ባሻገር የተለየ ቁም ነገርን ያዘለ ቃል ይሆናል። ማለትም ስልጣን መያዙንና ንግስናውን የሚያመላክት ነው ዙፋን ላይ መቀመጡ ባይረጋገጥ እንኳ።
✧የአረበኛ ቋንቋ ምሁር ኢማም አልፈዮሚይ እንዲህ ይላሉ፡
ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻋﻠﻰ ﺳﺮﻳﺮ ﺍﻟﻤﻠﻚ : ﻛﻨﺎﻳﺔ ﻋﻦ ﺍﻟﺘﻤﻠﻚ ﻭﺇﻥ ﻟﻢ ﻳﺠﻠﺲ ﻋﻠﻴﻪ
"በንግስና ዙፋን ላይ ተቀመጠ ሲባል ባይቀመጥበትም እንኳን ስልጣንን መጎናፀፉን ለማመላከት ነው።"
ስለዚህ ይህንን አንቀፅ በጥሬው ቀጥተኛውን ትርጉም በመያዝ ለመተርጎም መጣደፍ አደገኛ እና የጥሜት አካሄድ መሆኑ ታውቆ እጅጉን ሊወገዝ ይገባል። [አሏህ ከሃዲዎች ከሚሉት ሁሉ የጠራ ነው።]
በዚህና መሰል አሻሚ አንቀፆች ዙሪያ ልንይዘው የሚገባ አቋም አሏህን ከጉድለት፣ ከመመሳሳል ፣ እንዲሁም ከፍጡራን አገላለፅና አካላዊ ትርጓሜ ከማጥራት ጋር ለርሱ ልእልና በሚገባ መልኩ ማፅደቁ ግዴታ ነው።

✧ ኢማም አቡ ሐኒፋ እንዲህ ይላሉ፦
ﻭﻧﻘﺮ ﺑﺄﻥ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻠﻰ ﺍﻟﻌﺮﺵ ﺍﺳﺘﻮﻯ ﻣﻦ ﻏﻴﺮ ﺃﻥ ﻳﻜﻮﻥ ﻟﻪ ﺣﺎﺟﺔ ﺇﻟﻴﻪ ﻭﻻ ﺍﺳﺘﻘﺮﺍﺭ ﻋﻠﻴﻪ ﻓﻠﻮ ﻛﺎﻥ ﻣﺤﺘﺎﺟﺎ ﺇﻟﻰ ﺍﻟﺠﻠﻮﺱ ﻭﺍﻟﻘﺮﺍﺭ ﻓﻘﺒﻞ ﺧﻠﻖ ﺍﻟﻌﺮﺵ ﺃﻳﻦ ﻛﺎﻥ ﺍﻟﻠﻪ؟ ! ﺗﻌﺎﻟﻰ ﺍﻟﻠﻪ ﻋﻦ ﺫﻟﻚ
«አሏህ በአርሽ ላይ ኢስቲዋእ ማድረጉን እናረጋግጣለን፤ (ኢስቲዋኡ) በአርሽ ፈላጊ ሳይሆን ፤ በርሱ ላይም ሳይደላደል ነው። ከመቀመጥ እና ከመደላደል ፈላጊ ቢሆን ኖሮ ከዐርሽ በፊት ዬት ነበረ ሊባል ነው?! አሏህ ከዚሁ የላቀ ነው!።» [አል ወሲያ ገፅ /70]

✧ኢማም አልበይሀቂይ እንዲህ ይላሉ፦
ﻳﺠﺐ ﺃﻥ ﻳُﻌﻠﻢ ﺃﻥ ﺍﺳﺘﻮﺍﺀ ﺍﻟﻠﻪ ﺳﺒﺤﺎﻧﻪ ﻭﺗﻌﺎﻟﻰ ﻟﻴﺲ ﺑﺎﺳﺘﻮﺍﺀ ﺍﻋﺘﺪﺍﻝ ﻋﻦ ﺍﻋﻮﺟﺎﺝ ، ﻭﻻ ﺍﺳﺘﻘﺮﺍﺭ ﻓﻲ ﻣﻜﺎﻥ ، ﻭﻻ ﻣﻤﺎﺳﺔ ﻟﺸﻲﺀ ﻣﻦ ﺧﻠﻘﻪ ، ﻟﻜﻨﻪ ﻣﺴﺘﻮ ﻋﻠﻰ ﻋﺮﺷﻪ ، ﻛﻤﺎ ﺃﺧﺒﺮ ﺑﻼ ﻛﻴﻒ ، ﺑﻼ ﺃﻳﻦ ،
«ግዴታ መታወቅ ያለበት የአሏህ ኢስቲዋእ ከጠምዛዘነት መስተካከል እንዳልሆነ ፣ በቦታ መደላደልም እንዳልሆነ፣ ከፍጥረቱ ኣንዱም ጋር በመነካካትም እንዳልሆነ ነው። ነገር ግን በዐርሹ ላይ ኢስቲዋእን ኣደረገ ፤ እርሱ ባሳወቀን መልኩ ያለ ከይፊያ(እንዴታ) ፣ ያለ ቦታ » [አል ኢዕቲቃድ] ገፅ/72

የአሏህን "አስማእ እና ሲፋት" እናፀድቃለን በሚል ስለ አላህ የሚነገሩ እውነታዎችን ሁሉ ፍጡራን ላይ በሚያዩቸው ግንዛቤዎች የሚተረጉም እውር አስተሳሰብ ነው። አላህ ይጠብቀን!
በዚህም "ኢስባት" ማድረግን የግድ በአካላዊ ትርጓሜ ከልሆነ በስተቀር አይሆንም የሚል የጥሜታዊ አስተሳሰብ ነው።
በአንቀፁ ላይ የወረደ ቃል ብዙ ትርጉሞችን ያዘለ (ሙተሻቢህ) ሆኖ ሳላ በቀጥተኛው ካልተተሮገመ ብሎ ግግም ማለት ለምኑ ይሁን??
☞ የታዘዝነው ሙተሻቢህን ወደ ሙሕከም በመመለስ ሙሕከም ከሆነው ጋር በሚስማማ መልኩ መቶርገም ነው እንጂ በተገላቢጦሾ አይደለም።
ምክኒያቱም : አሏህ ሙሕከም የሆኑት አንቀፆችን ﺃﻡ ﺍﻟﻜﺘﺎﺏ
በማለት ገለጿቸዋል። ማለትም የቁርኣን ዋና እና መመለሻ ናቸው።
"አሏህ በቁርኣን የተናገረውን ለማፅደቅ ከተባለ":
ታዲያ ለማፅደቅ ሲባል የግድ በቀጥታው መቶርገም አለበት ?!
በግልፅ በቁርኣን ላይ በፍጡራን አገላለፅ እና ከጉድለት የጠራ እንደሆነ ተቀምጦ ሳለ… ግልፅ(ሙሕከም) እና የማያሻማ አንቀፅን ችላ ብሎ ትርጉም አልባ አድርጎ የተለያዩ ትርጉሞችን የያዘ አንቀፅ ላይ የሙጥኝ ብሎ በቀጥተኛውን ትርጓሜ ለመተርጎም መሟጋት ለምን?
ይህ እውን " ልበ–እውርነት" እና በዝንባሌና በተሽቢህ መጠመድ አይደለምን?
አሏህም «እነዚያ ልባቸው የጠመሙ ሙተሻቢህ የሆኑ አንቀፆችን ይከታተላሉ» ያለን እነዚህ አይደለምን?!
የግድ እያንዳንዱ አንቀፅ በቀጥታው መቶርገም አለበት የሚል መርህስ ከዬት የመጣ ነው።?
በዚህ የተጣመመ አካሄድ የምንሄድ ከሆነ ምን ያክል አስቀያሚ የጥመት አረማመድ መሆኑን ለመረዳት:
ይህንነ አንቀፅ ልብ እንበል …
አሏህ በቁርኣን እንዲህ ይላል፦
ﻭَﻣَﺎ ﻛَﺎﻥَ ﺭَﺑُّﻚ ﻧﺴِﻴّﺎً
ትርጉም፦ «ጌታህ ራሺ አይደለም» በማለት አሏህ በግልፅ ራሱን ከመርሳት አጥራርቷል።
በሌላ አንቀፅ ደግሞ እንዲህ ይላል፦
ﻓَﺎﻟﻴَﻮْﻡَ ﻧَﻨْﺴَﺎﻫُﻢْ ﻛَﻤَﺎ ﻧَﺴُﻮﺍ ﻟِﻘَﺎﺀَ ﻳَﻮْﻣِﻬِﻢْ
ﻫَﺬَﺍ
⇨ጥንቃቄ! ( ﻧﻨﺴﺎﻫﻢ ) የሚለው በቀጥተኛው ቢተረጎም= «እንረሳቸዋለን» የሚል ትርጉም ይሰጣል… ታዲያ አሏህ ራሱን በግልፅ ያጠራበት (መርሳት) በህሪን… "በቁርኣን የመጣውን ለማፅደቅ በቀጥታው መተርጎም አለበት!" በሚል ያንን አንቀፅ ችላ በማለት አሏህ በ"መርሳት" ይገለፃል ይባላልን??
☞( ﻧﻨﺴﺎﻫﻢ )
የሚለው ትርጉም ኢብኑ ዐባስ እንዳሉት፦
«በቅጣታቸው ውስጥ እንተዋቸዋለን» ማለት ነው።
ታዲያ ቀጥተኛው ትርጉም በመውሰድ ብቻ "ማፅደቅ" ይረጋገጣል ተብሎ አንቀፁ የሚያስተላልፈውን ትርጉም ማዛባት ( ﺗﺤﺮﻳﻒ) ማድረግ ተገቢ ነውን?!
ይልቅ… ይህንን አንቀፅ በቀጥታው መተርጎም ያንን "ሙሕከም" የሆነው አንቀፅን ትርጉም አልባ ማድረግ ነው።
# ክፍል (2) « ይቀጥላል»…
5.7K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-07 11:01:14
የእሜታችን ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) ቀብር ሳይፈርስ በፊት
------------
Ethio mewlid ኢትዮ መውሊድ
@ethiomewlid
3.8K views08:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2020-06-06 19:27:35
3.6K views16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ