Get Mystery Box with random crypto!

“ማረጋገጫ ከተሰጠን ጦርነቱን አቁመን ሀገር ለቀን ለመውጣት ዝግጁ ነው” የህወሃት አመራሮች ጦርነ | 💚💛❤️ ዮቶራዊያን💚💛❤️

“ማረጋገጫ ከተሰጠን ጦርነቱን አቁመን ሀገር ለቀን ለመውጣት ዝግጁ ነው” የህወሃት አመራሮች

ጦርነቱ ወደ መገባደዱ መድረሱን ተከትሎ የህወሃት ቁንጮዎች አነጋጋሪ ውሳኔ ላይ እንደ ደረሱ ከውስጥ አዋቂ የሚመጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ። ከቀን ወደ ቀን፣ ከሰዓት ወደ ሰዓት የከበባው ቀለበት በሁሉም አቅጣጫ እየጠበበ መምጣቱን የተረዱት የህወሃት ሰዎች አለም አቀፉ ማህበረሰብና የአፍሪካ ህብረት መውጫ ካመቻቸልን ጦርነቱን ወዲያው አቁመን ከሀገር ለመውጣት ተዘጋጅተናል የሚል አቋም ላይ እንደደረሱና ይሄንንም አቋማቸውን በቴድሮስ አድሃኖም አማካኝነት ለአሜሪካና የአውሮፓ ህብረት ተደራሽ እንዳደረጉ ታውቋል። ዛሬ የአፍሪካ ህብረት ያወጣውን መግለጫ ተከትሎ የህወሃት ሚዲያዎች በሙሉ ተኩስ አቁሙን እንደተቀበሉ ተደርጎ እንዲሰራጭ ከማዕከል ትዕዛዝ ተሰጥቷል።

ዛሬ ቴድሮስ አድሃኖም በርሊን ላይ ይህንኑ የህወሃት አመራሮችን ማስመለጫ መንገድ በተመለከተ ከተለያዩ ሰዎች ጋር እንደተነጋገረና በቀጣይ ቀናትም ወደ ብራሰልስ እንደሚጓዝ ይጠበቃል። ዛሬ በርሊን ላይ ካነጋገራቸው አካላት መካከል የአሜሪካ ሰዎችም እንደሚገኙበት ነው ጀርመን ካሉ ዲፕሎማሲያዊ ምንጮች የተረዳነው።

ጦርነቱ መቀልበስ የማይችልበት ደረጃ ላይ መድረሱን ጠላትም ወዳጅም ተረድቷል። አሁን መፍትሄው፣ ውሳኔውም ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ እጅ ነው። መከላከያ ሰራዊት ግዳጁን በሚገርም ኦፕሬሽን አፈፃፀም እየተወጣ ነው። ህወሃት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መወገዱ የማይቀር ብቻ ሳይሆን በጣም በፍጥነት የሚሆን ነገር መሆኑ ተረጋግጧል። ከአሁን በኋላ ከህወሃት በኋላ የሚኖረው የትግራይ ክልል አስተዳደርና የሰሜኑን የሀገራችን ክፍልን መልሶ ማቋቋም ላይ ትኩረት መደረግ አለበት!

    ( ሱሌማን አብዴላ )