2022-04-19 20:54:30
#Update
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ፤ ከክልሉ ተጨማሪ ወደ መንግስት ዩኒቨርሲቲ እንዲገቡ የተወሰነላቸው 4339 ተማሪዎች በምን አግባብ እና በምን ሂደት እንደሚመረጡ አሳውቋል።
4,339 ተማሪዎች 50 ፐርሰንት እና ከዛ በላይ ካመጡ ከክልሉ ሁሉም ዞኖች መካከል በውጤታቸው ቅደም ተከተል ይመረጣሉ ብሏል።
ይህ በዚህ እንዳለ ሌሎች 50 ፐርሰንት እና በላይ ውጤት አምጥተው ወደ ዩኒቨርስቲዎች መግባት ያልቻሉት ደግሞ በክልሉ መምህራን ኮሌጆቾ " በመደበኛው የዲግሪ ኘሮግራም " የመምህርነት ስልጠና እንዲጀምሩ ሰፋ ያለ ቁጥር ለመቀበል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ቢሮው አሳውቋል።
ሌላው የመግቢያ ነጥብ ያላመጡ ተማሪዎች በመደበኛ ተማሪነት በድጋሜ ፈተና ይወስዳሉ የተባለው ሁሉንም የክልሉን ተማሪዎች የሚያካትት ሲሆን ይህም በልዩ ሁኔታ ለአማራ ክልል ብቻ መሆኑ ተገልጿል።
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ወደ ዩኒቨርስቲዎች ሆነ ወደ መምህራን ኮሌጆቾ መግባት ያልቻሉት ተማሪዎች በቂ ዝግጅት አድርገው መፈተን እንዲችሉ የ2014 ዓም የ12ኛ ክፍል የፈተና ጊዜ እንዲራዘም ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቋል።
ትምህርት ሚኒስቴርም ቢሮው ባቀረበው ጥያቄ መሠረት ከመስከረም 2015 ዓ/ም በፊት ፈተናው እንደማይሰጥ ትላንት መወሰኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
የክልሉ ተማሪዎች የ2014 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከመስከረም 20 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ባሉት ጊዚያት ሊሰጥ እንደሚችል አውቀው ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ ቢሮው አሳስቧል።
መረጃውን ይፋ ያደረጉት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ማተብ ታፈረ ናቸው።
Join
@ethiolearn
@ethiolearn_bot
Contact
@Ethio_E_learning_center_Bot
5.2K views17:54