Get Mystery Box with random crypto!

የፈለገውን ያህል ብትሰራ የሰው ልጅ ስምህን ለማጠልሸት አንድ ስህተት ይበቃዋል ። የሚገርመው የቅፅ | ስብዕናችን #Humanity

የፈለገውን ያህል ብትሰራ የሰው ልጅ ስምህን ለማጠልሸት አንድ ስህተት ይበቃዋል ። የሚገርመው የቅፅበት ስህተትህን የዘላለም ባህሪህ አድርጎ አንተ ራሱ እስኪገርምህ በርቱዕ አንደበቱ ቀምሞ ያቀርብልሃል፣ ታሪክህን ጨርቅህ ላይ  ስምህን ልብስህ ላይ ለማንበብ ይሽቀዳደማሉ፣ጉድፍህንና ነቀፋህን ለሚከታተሉ ብዙ ቦታ አትስጥ፣ ለእነርሱ አንተ በውሃ ላይ መራመድ ብትችል እንኳ አስማት እንጂ ቅድስና አይመስላቸውም፣ እንዲያውም ዋና ስለማይችል ነው ሊሉህ ይችላሉ፣አለም እንደዚህ ናት ለስኬትህ ሳይሆን ለውድቀትህ ትፈጥናለች።

እኔ ትንሽነቴን አልረሳም ማወቄም አያመፃድቀኝም ።እኔ  የእናንተ የመምጣት እና መሄድ አሻራ ነኝ ፣ የእኔ መጉደል መጉደላቸሁ  እንከናችሁም አንከኔ  ነው፡፡ ጀግና ማለት ታግሎ የጣለ ሣይሆን ታግሎ ያለፈ ነው። ሁሌም ቢሆን እራስህን ተመልከት። የምትወድቀው ሌላውን ለመጣል የሞከርክ ቀን ነው፣ልትጥለው የሞከርከው ሰው ግን ገልብጦህ ከላይ ሆኖ ታገኘዋለህ።ሰው ምንም ብልህና አዋቂ ቢሆን በራሱ ሥራ ብቻ ራሱን ችሎ እንደማይኖር ዕወቅ:: ነገር ግን ሁሉም በየሥራው ጸንቶ እርስ በርሱ በሥራ ይፈላለጋል:: ስለዚህ ሰውን ሁሉ አክብረህ ኑር እንጂ ሰውን አትናቅ ሥራውንም አትንቀፍ::

ሁሉንም በገንዘብ እገዛዋለው ብለህ አታስብ በገንዘብ የምትገዛው ርካሹን ነገር እንጂ ውድ ነገሮች የዋጋ ተመን የላቸውም።የዋህነት እና ንፁህነት በእውቀት ብዛት ወይም በጥበብ ጥልቀት ተፈልጎ የማይገኝ በራሱ ንፁህ ስጦታ ነው፡፡ በገንዘብ የማይገዛ፤ በሀይልም የማይጠፋ፤በመከራም የማይደበዝዝ ለተወደደ የሚሰጥ የፈጣሪም ችሮታ ነው፡፡ 

        ለፍቅራችን፣ ውብ ቅዳሜ!

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot