Get Mystery Box with random crypto!

ሕይወት በ’የኔ’ እና ‘የኛ’ የምናሳንሰው ነገር የላትም… ከጽንፍ አልባው ምልዓት ላይ በተገለጸልን | ስብዕናችን #Humanity

ሕይወት በ’የኔ’ እና ‘የኛ’ የምናሳንሰው ነገር የላትም… ከጽንፍ አልባው ምልዓት ላይ በተገለጸልን ልክ የገባንን ሁሉ የእኔ/ኛ አንልም… እኛ ራሳችንን ያንን ምልዓት አይደለን? “You are not a drop in the ocean; you are the entire ocean in a drop” ይላል Rumi

ይህን ሁለንተና በግላዊነት መያዝ አይቻልም… የኔ ብሎ ማሳነስ አይቻልም… እኛው ራሳችን ሁለንተናውን ነንና ፣ ብዙ የአለማችን እሳቤዎች ከሕይወት በተናጥሎ የመኖርን ቅዠት ይሰብካሉ… ውቅያኖሱን ሆነህ ሳለ የውቅያኖሱን ‘አንድ ጠብታ ወስደህ’ የኔ ማለት ከራስም ያሳንሳል…ከራስህ ተነጥለህ ‘የራስህ’ ሊኖርህ አይችልም።

የግዙፍ ውቅያኖስ አካል ነን ፣ከኔ ቤት ላይ የረጨኸው እሳት ከሆነ ነበልባሉ ያንተን ቤት ይነካል ሽቶ ስትረጨኝ የመዓዛው ቅንጣቶች ለአፍንጫህ ውብ ጠረን ይለግሳል ሰው የዘራውን ያንኑ ደግሞ ያጭዳል ይህን ምስራቃውያኑ Karma ሲሉት ሌሎች ደግሞ Boomerang ይሉታል Boomerang አውስትራሊያኖቹ አቦርጂኒስቶች ከእንጨት የሚሰሩት ደጋን ቅርጽ ያለው የአደን መሳሪያ ሲሆን ወርዋሪው ዘንድ ተመልሶ እንዲመጣ ተደርጎ የሚነደፍ ነው… ለሃሳብ፣ ለስሜትና ድርጊትህ መጠንቀቅ የሚኖርብህ ወላፈኑ ‘ለእኔም’፣ ‘ለእርሷም’፣ ‘ለእነርሱም’ እንደሚተርፍ በማሰብ ነው ምክንያቱም We are all One!

በረከት በላይነህ "የመንፈስ ከፍታ" ላይ እንዲህ ይለናል
“የግልህ ወንዝ ስለሌለህ ብቻህን የምትሰራው ድልድይ የለም! የሰማዩ ርቀት፣ የምድሪቱ ስፋት በ’እኛ’ እንጂ በ’እኔ’ አይለካም፡፡ ውዱ ‘እኔ’ ከ’እኛ’ የተሰራው ነውና!”

ደምስ ሰይፉ

           ውብ አሁን!!

@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanityBot