መስጠት ካልቻልኩ መቀበል አይሆንልኝም "
ደግነት ልቤ ውስጥ በተዘራ ጊዜ ፍሬውን አጭጄ እሰበስብና ለተራቡት እሰጣቸዋለሁ . . .ነፍሴ የወይን ፍሬ ባበቀለች ጊዜ ፍሬዎቹን ጨምቄ የተጠሙትን አጠጣቸዋለሁ ::
ውስጤ በብርሃን በተሞላች ጊዜ የውስጤን ፋኖስ የመስኮቴ ጫፍ ላይ አስቀምጣትና በጨለማ ለሚጉዋዙት ብርሃን እሆናቸዋለሁ :: ጥላቻን ከልቤ ያጠፋልኝ ዘንድ ሁልጊዜም የፍቅርን ችቦ መጨበጥ እሻለሁ ::
ሰዎች በዘርና በቀለም ተለያይተው በተለያዩ አህጉራትና ሀገራት ይኖራሉ ,,,,, እኔ ግን ለሁሉም ማህበረሰቦች እንግዳ ነኝ ከየትኛውም ሀገር አልወግንም። መላው ዓለም ሀገሬ ነው፣
የሰው ልጅ ሁሉ ወገኔ ነው ።
የአዳም/አደም ልጆች ደካማ ሆነው በተለያዩ ጉዳዮች መከፋፈላቸው የሚያሳዝን ነው , ዓለም ሳትከፋፈልም ጥብብ ያለች ናት ይህችን ጠባብ ዓለም በግዛት ፣ በሰፈር፣በአውራጃ መከፋፈሉ በአላዋቂነት የታጀበ ሞኝነት ይመስለኛል . . . . !
"ካህሊል ጂብራን"
ውብ ምሽት
@EthioHumanity
@EthioHumanity
@EthioHumanityBot