Get Mystery Box with random crypto!

ከተለመደው ወጣ በሉ! አብዛኛው ሰው ለገጠመኙ የሚሰጠውን ምላሽ አትከተሉ፡፡ ከተለመደው ወጣ በሉ! | ስብዕናችን #Humanity

ከተለመደው ወጣ በሉ!

አብዛኛው ሰው ለገጠመኙ የሚሰጠውን ምላሽ አትከተሉ፡፡ ከተለመደው ወጣ በሉ! ለየት በሉ!

ድክም ሲላችሁ ተስፋ መቁረጥን ሳይሆን ማረፍን ልመዱ፡፡

ሰዎች ትተዋችሁ ሲሄዱ እነሱን ሲከታተሉ መጦዝን ሳይሆን ለብቻችሁ ጊዜን መውሰድን ልመዱ፡፡

•  ስሜታችሁ ሲረበሽ “ለምን ስሜቴ ተረበሸ” ብላችሁ የበለጠ መረበሽን ሳይሆን ተረጋግታችሁ መንስኤውንና መፍትሄውን ማግኘትን ልመዱ፣ ስትሳሳቱ ራስን መውቀስና በጸጸት ታስሮ መኖርን ሳይሆን ራስን ይቅር በማለትና ከሁኔታው ትምህርትን በማግኘት እንደገና መሞከርን ልመዱ፡፡

አብዛኛውን ግዜ ሰዎች የሚረበሹት በሚያጋጥማቸው ችግር እውነተኛ ባህሪ ሳይሆን ለችግሩ በሰጡት የስሜት ትርጉም የተነሳ ነው ። ዋናው ችግር በሕይወትህ የሚያጋጥምህ ችግር ሳይሆን ስለችግሩ የምትሰጠው ስሜት ነው ። በሕይወትህ የሚያጋጥሙህ ችግሮች ሁሉ እውነተኛ ክስተቶች አይደሉም ።

አብዛኞቹ የስሜትህ ሁኔታ ናቸው ። ትልቁ ችግር ከክስተቶቹ በመነሳት በራስህ ስሜት የምትፈጥራቸው ችግሮች ናቸው ። "

በሁኔታዎች አትወሰዱ! ከሁኔታዎች ውስጥ መልካም ነገርን መውጣት ልመዱ! ይለመዳል!

ዶ/ር እዮብ ማሞ

ውብ ቅዳሜ
@EthioHumanity
@EthioHumanity

@EthioHumanitybot