Get Mystery Box with random crypto!

አሜሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ በሁለቱ ሃገራት ግንኙነትና በቀጠናዉ ሰላም ዙሪጣ መክረዋል፡፡ የአሜሪካ | Ethio Fm 107.8

አሜሪካ እና ሳዑዲ አረቢያ በሁለቱ ሃገራት ግንኙነትና በቀጠናዉ ሰላም ዙሪጣ መክረዋል፡፡

የአሜሪካዉ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከሳኡዲዉ ልኡል ጋር ተገናኝተዉ መነጋገራቸዉ ተገልጿል፡፡

ዉጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ በእስራኤል፣ የመን፣ ሱዳን ጉዳይ እና በሰብዓዊ መብቶች ዙሪያ ግልጽ እና የተሳካ ንግግር ከልኡል ሞሀመድ ቢን ሳልማን ጋር ማድረጋቸዉን የአሜሪካ መንግስት ነዉ የገለጸዉ፡፡

ከተወያዩባቸዉ ጉዳዮች መካከል ሳዑዲ እና እስራኤል ያላቸዉን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ወደ መልካም መመለስ አንዱ ቢሆንም ሳዑዲ ግን ለዚህ ቅድመ ሁኔታን አስቀምጣለች፡፡

የፍልስጤም ዘላቂ ደህንነት እና የሳዑዲ የኒኩሌር ፕሮግራም ማዘጋጀት ቅድመ ሁኔታዎቹ ሆነዉ ተቀምጠዋል፡፡
የአሜሪካዉ ዉጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጉብኝት ሳዑዲ አረቢያ የአረብ-ቻይና ኢንቨስትመንት ኮንፍረንስ ሊካሄድ ሁለት ቀናት ሲቀሩት የተደረገ መሆኑን አርቲ ኒዉስ ዘግቧል፡፡

በእስከዳር ግርማ

ሰኔ 01 ቀን ቀን 2015 ዓ.ም

ለታማኝና ወቅታዊ መረጃዎች ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

YouTube https://www.youtube.com/.../UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos