ሁዋዌ በቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኢንስቲትዩት የአይሲቲ ስልጠና ማዕከሉን አስጀመረ። ማዕከሉ ተማሪዎች በኢንስቲትዩቱ ከሚሰጣቸው መደበኛ ስልጠና በተጨማሪ ክህሎት የሚጨብጡበት ይሆናል ተብሏል። የስልጠና አሰጣጡ የገጽለገጽ እና የonline አማራጮች እንዳሉት ተገልጿል። በኢንስቲትዩቱ የ HUAWEI ICT Academy የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት አስተባባሪ ቤተልሔም መስፍን፥ በማዕከሉ የሚሰጥ ስልጠና በአገሪቱ የቴሌኮም ዘርፍ ያሉ የሙያተኞች ፍላጎት ለመሙላት ጉልህ ድርሻ ይኖረዋል ብለዋል። ሁዋዌ በኢትዮጵያ ከ43 በላይ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር እየሠራ የሚገኝ ሲሆን የሚሰጠውን ስልጠና በብቃት ለሚያጠናቅቁ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ይሰጣል። @Ethio_Students_only @Ethio_Students_only @Elshio_ACADEMY 425 viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, 16:11