#RayaUniversity በትግራይ ከሚገኙት 4ቱም ዩኒቨርሲቲዎች ውጭ ተመድባቹ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት መማር ላልቻላቹህ መደበኛ ተማሪዎች በሙሉ ራያ ዩኒቨርሲቲ በሀገራችን ከሚገኙ አራተኛው ትውልድ ዩኒቨርሲቲዎች መካከል አንዱ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲያችን ከመቸውም ጊዜ በላይ በተጠናከረ መልኩ ስራዎችን ለማከናወን በዝግጅት ላይ ይገኛል፡፡ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት በተመደባችሁበት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታችሁ መከታተል ያልቻላቹህ ከ2ኛ-5ኛ ዓመት ተማሪዎች በሙሉ በራያ ዩኒቨርሲቲ ከታች በተዘረዘሩት 23 የትምህርት ክፍሎች ብቻ መማር የምትፈልጉ በስራ ሰዓት ከ 17/08/2015 እስከ 20/08/2015 ዓ.ም ባሉት የስራ ቀናት በስልክ ቁጥር 09-70-14-00-00 09-70-24-00-00 09-70-23-00-00 ለራያ ዩኒቨርስቲ ሬጅስትራር እየደወላችሁ እንድትመዘገቡ እናሳውቃለን። ራያ ዩንቨርሲቲ @Ethio_Students_only @Ethio_Students_only @Elshio_ACADEMY 693 viewsElshio Owner,Ethio Students Admin, edited 16:16