Get Mystery Box with random crypto!

#ማስታወቂያ የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም ለምርምር ጆርናል ባለቤቶችና ለሀገር ውስጥ ከፍተኛ | Ministry of Education Ethiopia

#ማስታወቂያ

የካቲት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

ለምርምር ጆርናል ባለቤቶችና ለሀገር ውስጥ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፣ ለምርምር ተቋማት እና ሙያ ማህበራት

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር በሀገር ውስጥ የሚታተሙ የምርምር ጆርናሎች ጥራትና እይታን ለማሳደግ ሲባል የምዘናና እውቅና አሰራር ስርአት መዘርጋቱ ይታወቃል፡፡

ስለሆነም ከተመሰረተ 3 አመት የሞላቸው ጆርናሎችን የምታስተዳድሩና የእውቅና አሰጣጥ መመሪያ Amended Guideline for Evaluation of Journals Published in Ethiopia No.: Research 01/2019) መስፈርቶችን የምታሟሉ ተቋማት በጆርናሉ ዋና አርታኢ በኩል ይህ ደብዳቤ ከወጣበት ቀን አንስቶ በአስራ አምስት (15) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ

በhttp://survey.ethernet.edu.et/index.php/888858?lang=en

የተቀመጠውን ቅጽ በመጠቀም እንድታመለክቱ ጥሪ እያደረግን ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ
ethiojournalaccreditation@ethernet.edu.et

በመላክ መረጃ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ
ይህ ማስታወቂያ በ2015 ዓ.ም አራተኛ ዙር ያመለከቱትንና ለዳግም እውቅና አመልክተው ፍተሻው በሂደት ላይ ያሉትን ጆርናሎች አይመለከትም፡። ይሁን እንጂ የግምገማ ውጤቱ እንደታወቀ መስፈርቱን ባለማሟላት እውቅና ለማያገኙ አመልካቾች ሚ/ር መስሪያ ቤቱ ወደፊት በልዩ ሁኔታ የሚያስተናግድ መሆኑን እንገልጻለን፤

ማንኛውም አመልካች የሀገር ውስጥ ጆርናሎች ፍተሻ እና እውቅና አሰጣጥ Amended Guideline for Evaluation of Journals Published in Ethiopia No.: Research 01/2019) መስፈርቶችን ማሟላት ይጠበቅበታል፤

ትምህርት ሚኒስቴር