በሀዋሳ ከተማ በሺህዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች አደባባይ በመውጣት የተመሳሳይ ፆታ ግንኙነትንና ውርጃን በሠላማዊ ሰልፍ አወገዙ ፡፡ ሠልፈኞቹ ድርጊቶቹን ያወገዙት በከተማው ዋና ዋና ጎዳናዎች በመዘዋወርና የተለያዩ መፈክሮችን በማሰማት ነው። የተቃውሞ ሰልፉን ያስተባበሩት በሃዋሳ ከተማ የሚገኙ 22 የቃለሕይወት አብያተ ክርስትያን ናቸው። በሃዋሳ ዩኑቨርሲቲ የህግ መምህር እና ተመራማሪ አቶ ብርሃኑ ገኔቦ በኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ የተመሳሳይ ጾታ ግኑኝነት ከበድ ያለ ቅጣት እንደሚያስከትል ገልጸዋል። Via DW @sheger_press @sheger_press 10.6K viewsedited 16:52