የአማራ ክልላዊ መንግሥት የክልሉ ብልጽግና ፓርቲ ኃላፊና የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ አባል ግርማ የሺጥላ በሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ጓሳ በተባለ አካባቢ የተገደሉት "በታጠቁ ጽንፈኛ ኃይሎች" ነው ሲል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። "የጽንፈኛ ኃይሎችን የሽብር ድርጊት" ለማስቆም ርምጃ እንደሚወስድ የገለጠው የክልሉ መንግሥት፣ የግድያውን ፈጻሚዎች ለፍርድ አቀርባለኹ በማለት ቃል ገብቷል። ግርማ የተገደሉት፣ ከመንግሥትና የድርጅት ሥራ መልስ ከመሃል ሜዳ ከተማ ወደ ደብረ ብርሃን ከተማ ሲጓዙ እንደኾነ የክልሉ መንግሥት ጨምሮ ገልጧል። @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news 12.1K views04:50