Get Mystery Box with random crypto!

ጨዋታው በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ ኢትዮጵያ ግብጽን በአስደማሚ ሁኔታ 2 ለ0 አሸንፋለች | ETHIO-MEREJA®

ጨዋታው በኢትዮጵያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ግብጽን በአስደማሚ ሁኔታ 2 ለ0 አሸንፋለች!!

ለአፍሪቃ ዋንጫ ማጣሪያ ሁለተኛ የምድብ ግጥሚያውን ሐሙስ፤ ሰኔ 2 ቀን፣ 2014 ዓም ማላዊ ቢንጉ ብሔራዊ ስታዲየም ውስጥ ያካኼደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የግብጽ አቻውን 2 ለ0 አሸንፏል።

ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ግብ በ21ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠረው ዳዋ ሆቴሳ ነው። ሁለተኛውን ግብ ደግሞ በ40ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ ያሳረፈው ሽመልስ በቀለ ነው። ሁለቱም ግቦች የኢትዮጵያ አጥቂዎች ድንቅ ብቃት የታየበት ነው።

ኢትዮጵያ በአንደኛ ደረጃ የምድቡ መሪ ሆናለች።

እንኳን ደስ አላችሁ፣ አለን
T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja