Get Mystery Box with random crypto!

ተጠናቀቀ ሪያል ማድሪድ ሻምፒዮን ሆኗል ! የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በፈረን | ETHIO-MEREJA®

ተጠናቀቀ

ሪያል ማድሪድ ሻምፒዮን ሆኗል !

የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ በፈረንሳይ ርዕሰ መዲና ፓሪስ በሚገኘው ስታድ ዴ ፍራንስ ስታዲየም ሲካሄድ ሪያል ማድሪድ ከ ሊቨርፑል ጋር ያደረገውን ጨዋታ 1 - 0 በሆነ ውጤት አሸንፈዋል።

የሪያል ማድሪድን የማሸነፊያ ግብ ቪኒሰስ ጁኒየር አስቆጥሯል። ሪያል ማድሪድ ለአስራ አራተኛ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊ መሆናቸውን አረጋግጠዋል ።

ቪኒሰስ ጁኒየር በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ላይ ግብ ያስቆጠረ አምስተኛው በእድሜ ትንሹ ተጫዋች ሆኗል። ቪኒሰስ ጁኒየር በዘንድሮ የውድድር አመት በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ በአስር ግቦች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎን አድርጓል ።

ሊቨርፑል 0 - 1 ሪያል ማድሪድ
ቪኒስየስ ጁኒየር 59'

T.me/ethio_mereja
@ethio_mereja